Saturday, 23 April 2016 10:04

የኢቢሲ በርካታ ሰራተኞች ሥራለመልቀቅ አኮብኩበዋል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

“የሥራ ልምድ አፃፉ ማለት ሥራ ለቀቁ ማለት አይደለም
   የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በርካታ ሰራተኞች ከስራ ለመልቀቅ ማኮብኮባቸውን የአዲስ
አድማስ ምንጮች ገለፁ፡፡ በኢቢሲ 10ኛ ፎቅ ላይ የሚገኘው የስራ ልምድ ማፃፊያ ክፍል ሰሞኑን የስራልምድ በሚያፅፉ ሰራተኞች ተወጥሮ እንደሰነበተ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኢቢሲ የሚከፍለው ደሞዝ መጠን፣ ለሰራተኞች እንደ ትራንስፖርትና የመኖሪያ ቤት አበል አለመክፈሉና አጠቃላይ ለሰራተኛው የሚደረገው እንክብካቤ ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር ሲነፃፀር እጅግ አነስተኛ መሆኑ ሠራተኞቹ ከስራ ለመልቀቅ ምክንያት ሆኗቸዋል የሚሉት ምንጮች በአሁን ሰዓት የተሻለ ክፍያ የሚከፍሉ አማራጭ የሚዲያተቋማት እየተስፋፉ በመምጣታቸው የሰራተኛውልብ አኮብኩቧል ብለዋል፡፡ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ አንድ የኢቢሲጋዜጠኛ በሰጠው አስተያየት፤ ኢቢሲ በአመራርላይ ላሉ የተቋሙ ሰራተኞች የነዳጅ፣ የትራንስፖርትየሃላፊነትና የህክምና አበል እንደሚከፍል ገልፆስራውን በአብዛኛው ደክመው ለሚሰሩትና ውጣውረድ ለሚበዛባቸው የበታች ሰራተኞች እነዚህ ጥቅማ ጥቅሞች አለመሰጠቱ ሰራተኛው ሌላአማራጮችን እንዲመለከት እንዳደረገው ተናግሯል።ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩሉ፤ በተሰጠው የስራሃላፊነት ከሶስት አመት በፊት በተደረገለት ጥቂትየደሞዝ ጭማሪ ብቻ እስከዛሬ ድረስ እንደሚሰራጠቁሞ ያለ ጭማሪ፣ ያለ ጥቅማ ጥቅምና ያለእድገት በስራ ለመቀጠል ፍላጎት እንደሌለውና ሌላቦታ ለመወዳደር የስራ ልምዱን በእጁ ማስገባቱን
ገልጿል፡፡ሌሎቹ አስተያየታቸውን በጋራ የሰጡን የተቋሙሰራተኞች በበኩላቸው፤ ተቋሙ የተመረሰተበትን50ኛ ዓመት ሲያከብር 50ሚ. ብር በጀት ይዞለሰራተኞቹ መኖሪያ ቤት እንደሚያሰራ ቢገልፅምእስካሁን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አለማድረጉሌላው ሰራተኛው ተስፋ እንዲቆርጥና ከመስሪያቤቱ ለመልቀቅ እንዲነሳሳ ምክንያት እንደሆነተናግረዋል፡፡ እስካሁን በተገኘው መረጃ ብቻ ከ35በላይ ሰራተኞች የስራ ልምድ ማፃፋቸውንምምንጮች ጠቁመዋል፡፡ የእርከን እድገት አድርጉልን፣ጥቅማ ጥቅም ይታሰብልንና መሰል ጥያቄዎችንሰራተኛው በየጊዜው ቢጠይቅም ማኔጅመንቱምላሽ አለመስጠቱን ሰራተኞቹ ገልፀዋል፡፡ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የስራ ሃላፊ፤በዚህ መጠን ሰራተኛው የስራ ልምድ ስለማፃፉመረጃ እንደሌላቸው ጠቁመው፤ የስራ ልምድአፃፉ ማለት ስራ ለቀቁ ማለት እንዳልሆነ ገልፀዋል።ድርጅቱ የራሱ የሆነ የደሞዝ ስኬል፣ የደረጃእድገትና የደሞዝ እርከን ጭማሪ እንዳለውና ይህምበተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀ መሆኑን የገለፁትሃላፊው፤ አንድ ሰራተኛ በድርጅቱ ስኬል መሰረትደሞዝ እየተከፈለው ከዚያ እጥፍ ክፍያ ቢያገኝናየተሻለ ፍለጋ ቢሄድ ጥፋተኛ የሚባልበት ምክንያትየለም ብለዋል፡፡ ሃላፊው፤ እስካሁን ደሞዝ አነሰኝ፤እንዲህ አይነት ችግር ደርሶብኛል ተበድያለሁ ብሎያመለከተ ሰራተኛ እንደሌለና ምንም አይነት ቅሬታእንዳልቀረበም ጨምረው ገልፀዋል፡፡



Read 3778 times