Saturday, 16 April 2016 10:37

ኢትዮጵያዊቷ በኩዌት አሰሪዎቿን “በሰው በላነት” ከሰሰች

Written by 
Rate this item
(21 votes)

     በኩዌት በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ የምትሰራ ስሟ ያልተጠቀሰ ኢትዮጵያዊት፣ የአሰሪዎቿን  ቤተሰቦች የሰው ስጋ ይበላሉ ስትል መክሰሷን ገልፍ ዲጂታል ኒውስ የተባለው ድረገጽ ዘገበ፡፡ሳላዋ በተባለው የአገሪቱ አውራጃ በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ የምትሰራው ኢትዮጵያዊቷ፣ በአሰሪዎቿ   መኖሪያ ቤት ውስጥ የሰው ራስ ቅል ተደብቆ ማየቷን በመጥቀስ ለፖሊስ አቤቱታዋን ያቀረበች ሲሆን፣ የአካባቢው ፖሊስም ጉዳዩን ለማጣራት ወደ አሰሪዎቹ በሄደበት ወቅት፣ የቤቱን በር የሚከፍትለት ሰው ማጣቱን ዘገባው ገልጧል፡፡ ፖሊስ ጉዳዩን በመመርመር ላይ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ የምርመራ ቡድኑ ምናልባትም ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ከአሰሪዎቿ የደረሰባትን በደል ለመበቀል ያደረገቺው ድርጊት ሊሆን ይችላል፣ አልያም የአእምሮ ጤንነቷ የተዛባ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት መያዙን አስታውቋል፡፡

Read 6739 times