በዳንኤል ኢስፒኖዛ ዲያሬክት የተደረገው ፊልሙ፤ በደቡብ አፍሪካ የተቀረፀ ትእይንት ተካቶበታል፡፡ የ57 ዓመቱ ዴንዝል ዋሽንግተን በዚህ ዓመት ለእይታ የሚበቃ “ዘ ማትሪስ ሰርክል” በተባለ ፊልም ላይ እየሰራ ሲሆን “ፍላይት” የተባለው ሌላ ፊልሙ ከዓመት በኋላ እንደሚታይ ይጠበቃል፡፡
የ57 ዓመቱ ዴንዝል ዋሽንግተን በፊልም ትወና ሙያ ለ30 ዓመታት የሰራ ሲሆን ሁለት ጊዜ የኦስካር ሽልማት ወስዷል፡፡ ዴንዝል ከ40 በላይ ፊልሞችን መስራቱን የሚገልፀው የቦክስ ኦፊስ ሞጆ መረጃ፤ ፊልሞቹ በሰሜን አሜሪካ 1.94 ቢሊዮን ዶላር በመላው ዓለም ደግሞ 3.19 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘባቸው አመልክቷል፡፡