Saturday, 13 February 2016 11:31

”The Voice Within” የስዕል ትርኢት ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሰዓሊ ሮቤል ብርሃኔ ከ50 በላይ የሥዕል ስራዎች ለእይታ የሚቀርቡበት “The Voice Within” (የራስ ድምፅ) የተሰኘ የስዕል ትርኢት የፊታችን ማክሰኞ ከ11፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ሙዚየም ይከፈታል፡፡ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ለእይታ ክፍት ሆኖ ይቆያልም ተብሏል፡፡
ሰዓሊ ሮቤል ብርሀኔ፤ በዓሉ የስዕል ትርኢት ሲያቀርብ አራተኛ ጊዜው ሲሆን ከሌሎች ሰዓሊያን ጋር ከ20 ጊዜ በላይ በውጭና በአገር ውስጥ ለእይታ አብቅቷል፡፡ ሥዕሎቹ፤ ሰዎች ህሊናቸው እርስ በእርሱ ሲጋጭባቸው መልሱ በገዛ ህሊናቸው ውስጥ እንደሚገኝና ግጭቱም ከኋላ ታሪካቸው ጋር የተሳሰረ መሆኑን አጉልተው ያሳያሉ ተብሏል፡፡

Read 2547 times