Saturday, 13 February 2016 11:26

“የፍቅር ቀጠሮ” በዋሽንግተን ሆቴል ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(8 votes)

ይህ በዚህ እንዳለ፤ የፍቅረኞች ቀንን አስመልክቶ “የፍቅር ቀጠሮ” የተሰኘ ፕሮግራም ነገ በዋሺንግተን ሆቴል ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ተገለፀ፡፡
ፕሮግራሙ በኢትዮ ኤቨንትስ አስተባባሪነት፣ “ኢስት አፍሪካን ታይገር ብራንድስ” ከዋሺንግተን ሆቴል ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል ተብሏል፡፡
በምሽቱ ታዋቂ ድምፃውያን የሚያቀነቅኑ ሲሆን ጥንዶቹ በቀይ ምንጣፍ ስነስርአት አቀባበል ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡ በተለያዩ አዝናኝ ውድድሮች ላይ ለሚያሸንፉ ጥንዶችም የተለያዩ ሽልማቶች መዘጋጀታቸው ተጠቅሷል፡፡
በዲጄ ኪንግስተን የሚመራ የሙዚቃ ዝግጅት እንዲሁም የኮሜዲያን ፕሮግራም የሚቀርብ ሲሆን ለፍቅረኞቹ ራትና ወይንም መሰናዳቱን አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡
ፕሮግራሙ በቀጥታ በብስራት ኤፍኤም ሬዲዮ እንደሚተላለፍ የገለፀው የኢትዮ ኤቨንት ስራ አስኪያጅ አቶ ማናዬ እውነቱ፤ መግቢያ ለጥንዶች 1ሺህ ብር፣ ለነጠላ 500 ብር እንደሚከፈል ታውቋል፡፡

Read 3322 times