Saturday, 13 February 2016 10:49

በኩዌት በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ተጠየቀ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

- “ኢትዮጵዊቷ የአሰሪዋን ልጅ ገድላ፣ ራሷን ለማጥፋት ሞክራለች”
- በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለጉዳዩ በቂ መረጃ የለንም ብለዋል

     በኩዌት አንዲት ኢትዮጵያዊ የቤት ሰራተኛ፤ የአሰሪዋን ልጅ ገድላ ራሷን ለማጥፋት ሞክራለች መባሉን ተከትሎ፣ የአገሪቱ ፓርላማ አባል የሆኑት ሳዶን ሃመድ አል ኦታቢ መንግስት በኩዌት በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ አፋጣኝ ጥብቅ እርምጃ እንዲወስድ ለአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የአገር ውስጥ ሚኒስትር ጥያቄ ማቅረባቸው ተዘገበ፡፡
በአገሪቱ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ከዚህ ቀደምም በአሰሪዎቻቸው ላይ አሰቃቂ ግድያ ፈጽመዋል ያሉት አል ኦታቢ፣ መንግስት በኢትዮጵውያን የቤት ሰራተኞች ላይ ወደ አገራቸው መመለስ፣ የስራ ቅጥር ውላቸውን የማቋረጥና የመኖሪያ ፈቃዳቸው እንዳይታደስ ማገድን የመሳሰሉ አፋጣኝ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባዋል ማለታቸውን “አረብ ታይምስ” ትናንት ዘግቧል፡፡አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ የአሰሪዋን ልጅ በስለት ወግታ ከገደለች በኋላ ራሷን ወግታ ለመግደል ስትሞክር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏንና በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላት እንደሚገኝ የዘገበው “ኩዌት ታይምስ”፣ ፖሊስ ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝ ጠቁሟል፡፡ በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሞሃመድ ጉደታ በበኩላቸው፣ ኤምባሲው ጉዳዩን በተመለከተ በቂና ይፋዊ መረጃ እንዳልደረሰው ጠቁመው፣ ጉዳዩን የሚከታተል ተወካይ ወደ ኩዌት አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርና ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ወደምትታከምበት ሆስፒታል መላካቸውን እንደገለጹ ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 5788 times