Saturday, 06 February 2016 10:56

የመኢአድ ዋና መሪዎች፤ እርስበርስ “የእገዳ” ውሳኔ አስተላለፉ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

- በፊናቸው ጠቅላላ ጉባኤ እናካሂዳለን ብለዋል
- አንዱ ሌላውን “ከሃላፊነት አግጃለሁ” ሲሉ ወስነዋል

   የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት፤ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪን የከሰሰ ሲሆን፤ ፍ/ቤት አቶ አበባውን ለጊዜው በማገድ፣ የክስ መልስ እንዲያዘጋጁ የአንድ ወር ቀጠሮ ሰጠ፡፡  
ለአመታት ከተለያዩ ውዝግቦች እፎይታ ያላገኘው መኢአድ፣ ዘንድሮም የፓርቲው ፕሬዚዳንትና የምክትላቸው በተቀናቃኝ ጐራ የተሰለፉበት የተካረረ ውዝግብ ገጥሞታል፡፡
መኢአድ፤ መጋቢት 24 ቀን ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ ወስኗል ቢባልም፤ የፓርቲው  ም/ሬዚዳንት ተቃውመዋል፡፡ አቶ አበባው ከአመራር እንዲታገዱ ስለተወሰነ ጉባኤውን የመጥራት ስልጣን የላቸውም ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ አንድሪያስ ኤሮ፤ እኛ በስድስት ወር ጠቅላላ ጉባኤ እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
በአቶ እንድሪያስ ኤሮ አስተባባሪነት፤ ከ50 በመቶ በላይ የፓርቲው ላዕላይ ም/ቤት አባላት ተሰብስበው፤ አቶ አበባው መሃሪን ከፕሬዚዳንትነት አግደዋል፡፡ ክስም አቅርበዋል፡፡
አቶ አበባው በበኩላቸው ሌላ ስብሰባ በማካሄድ፤ የአቶ እንድሪያስን ቡድን አግጃለሁ ብለዋል፡፡ በፊናቸው ክስ እንደሚያቀርቡ በመጥቀስ፡፡

Read 3583 times