በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ከ30ሺህ በላይ ዜጐች በጭፍጨፋ ያለቁበት የሰማዕታት 75ኛው ዓመት መታሰቢያ ከነገ ወዲያ ይዘከራል፡፡ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም እንዳስታቀው እለቱን የሚዘክሩ ጥናታዊ የምርምር ሥራዎች በምሁራን የሚቀርቡ ሲሆን በአሉን አስመልክቶ አውደርእይ እና ሌሎች ዝግጅቶቹም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስደስት ኪሎ ዋነኛ ግቢ እዚያው አካባቢ በሚገኘው የሰማዕታት ሐውልትና በሌሎች ሥፍራዎች ይቀርባሉ፡፡ በዚሁ መሠረት ትናንት ከሰዓት በኋላ በኢትዮጵያ ጥናት ምርምር ተቋም አውደጥናት የተካሄደ ሲሆን የፖሊስ ሠራዊት ኦርኬስትራም ወኔ ቀስቃሽ ጣዕመ ዜማዎች በሥፍራው አሰምቷል፡፡