ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የተመሠረተበትን 90ኛ ዓመት በማስመልከት የዛሬ ሳምንት ተከፍቶ የነበረው ዓውደርእይ ዛሬ ይዘጋል፡፡ ከመጀመሪያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ገብረክርስቶስ ተክለሃይማኖት ጀምሮ እስካሁኗ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሙሉወርቅ ገብረሕይወት ድረስ 19 ሥራ አስኪያጆች በዘጠኝ አስርት ዓመታት ውስጥ ድርጅቱን በመምራት ከሀገሪቱ የሕትመት ታሪክ ውስጥ ጉልህ ድርሻ የነበረውን ማተሚያ ድርጅት መርተዋል፡፡ በአውደርእዩ የምስጢራዊ ሕትመቶችን፣ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን እና የኮሎኔል መንግስቱን ጉብኝት፣ የጋዜጦችን ሕትመትና ሌሎች እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ትዕይንቶች፣ ተካተውበታል፡፡