በ1984 ዓ.ም ማይክል ጃክሰን፣ በ2000 ዓ.ም ደግሞ ካርሎስ ሳንታና ስምንት የግራሚ ሽልማቶች በአንድ ምሽት ወስደው እንደነበር ይታወሳል፡፡ አርቲስቷ በከፍተኛ የአልበም ሽያጭ ገበያውን በሚመራው “21” የተሰኘ አልበሟ የ”ዓመቱ ምርጥ አልበም”፣ “ሮሊንግ ዲፕ” በሚለው ዘፈኗ የ”ዓመቱ ምርጥ ሪኮርድ” እና “ምርጥ ዘፈን” ያገኘቻቸው ሽልማቶች ትልቅ ግምት አስገኝተውላታል፡፡ “21” በሳምንት ሩብ ሚሊየን እየተሸጠ ለ20 ሳምንታት ገበያውን ሲመራ ቆይቷል፡፡ አዴሌ ሰሞኑን ለአምስት አመት ከሙዚቃ ኢንዱስትሪው እንደምትርቅ በመናገሯ ገበያው እንዳይቀዘቅዝባት የተፈራ ሲሆን በእረፍት ጊዜዋ ትዳር መስርታና ልጆች ወልዳ መነሳት እንደምትፈልግ ገልፃለች፡፡ በዘንድሮው 54ኛ ግራሚ “የዓመቱ ምርጥ የአር ኤንድ ቢ አልበም” ተብሎ የተሸለመው የክሪስ ብራውን “ፌም” የተሰኘ አልበም ነው፡፡ የካናዬ ዌስት “ማይ ቢውቲፉል ዳርክ ትዊስትድ ፋንታሲ” የዓመቱ ምርጥ የራፕ አልበም ተብሏል፡፡ “ዎክ” በተባለው ዜማ የዓመቱን ምርጥ የሮክ ሙዚቃ ያሸነፉት ፉ ፋይተርስ፤ “ዌስቲንግ ላይት” በተባለው አልበማቸው የዓመቱ ምርጥ የሮክ አልበም ሽልማትን አግኝተዋል፡፡