Saturday, 23 January 2016 13:19

የህትመትና ወረቀት ሥራዎች አለምቀአፍ ኤግዚቢሽን ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በህትመት፣ ወረቀትና እሽግ ሥራዎች ላይ ያተኮረና ከ40 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች የተሳተፉበት አለምአቀፍ ኤክስፖ ትላንት በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ፡፡
በፕራና ፕሮሞሽን ተዘጋጅቶ ከጥር 13-15 በሚቆየውና በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በዶ/ር መብራቱ መለስ በተከፈተው በዚሁ “አፍሪ ፕሪንት ኤንድ ፓኬጂንግ ኤክስፓ” ላይ፤ አታሚዎች፣ የህትመት መሣሪያ አስመጪዎች፣ የህትመት ማስታወቂያ ድርጅቶች፣  የወረቀት አምራቾችና አስመጪዎች፣ የግራፊክ ዲዛይን ድርጅቶች እንዲሁም ከወረቀት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን የሚሰሩ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች ተሣታፊ ሆነዋል፡፡
በኤክስፖው በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች የንግድ ትስስር እንዲፈጥሩና የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ ታስቦ መዘጋጀቱን የተናገሩት የፕራና ፕሮሞሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ነቢዩ ለማ፤ ፕሮግራሙ በአገራችን በዘርፉ ለተሰማሩ ድርጅቶ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል፡፡ በዚህ ኤክስፖ ላይ ለመሳተፍ ከአሜሪካ፣ ከአውሮፓና ከኤዥያ የመጡ ባለሀብቶችና የድርጅቶች ተወካዮች መኖራቸውንም አቶ ነቢዩ ተናግረዋል፡፡

Read 1793 times