Saturday, 23 January 2016 13:17

ሮተሪ ክለብ 25ኛ ዓመቱን ዛሬ ያከብራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሮተሪ ክለብ በአዲስ አበባ የተቋቋመበትን የ25ኛ ዓመት በዓል ዛሬ ያከብራል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማዕከል በሚከበረው በዚሁ በዓል ላይ የክለቡ አባላት፣ በጐ ፈቃደኞችና ታዋቂ ሰዎች ይገኙበታል ተብሏል፡፡
እ.ኤ.አ ፌቡራሪ 23 ቀን 1905 ዓ.ም በቺካጐ የተቋቋመው ሮተሪ ክለብ፤ በአሁኑ ወቅት በ200 አገራት ውስጥ የሚገኙ 33 ሺ ክለቦችንና ከ1.2 ሚሊዮን በላይ አባላትን ይዟል፡፡
ክለቡ በበጐ ፈቃደኛ አባላቱ አማካኝነት በመሠረታዊ ትምህርት አቅርቦት፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና፣ በበሽታ መከላከል፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃና በንፅህና አጠባበቅ እንዲሁም በማህበረሰብ ኢኮኖሚ ልማት ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡

Read 1786 times