Saturday, 02 January 2016 14:16

አሸባሪዎች ግጥምን ሁነኛ መሳሪያ አድርገውታል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

- የአልቃይዳው መሪ ስሜት ቀስቃሽ ግጥም ለሰልጣኞች ታድሏል
አልቃይዳን የመሳሰሉ አሸባሪ ቡድኖች ግጥምን ተጠቅመው የግለሰቦችን ልብ በማማለል አዳዲስ  አባላትን እየመለመሉ እንደሚገኙና የፕሮጋንዳ መሳሪያ እንዳደረጉት ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ሰሞኑን ያወጣውን የጥናት
ውጤት ጠቅሶ ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡ ታጣቂ ቡድኖቹ የግለሰቦችን ስነ ልቦና ለመቀየርና ስሜታቸውን ለመግዛት ግጥምን በመሳሪያነት  እየተጠቀሙ ነው ያለው ዘገባው፤ ይህም አላማቸውን ለማስረጽና አዳዲስ አባላትን ለማፍራት ሁነኛ መሳሪያና ስልት  እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ አልቃይዳ በየመን ግጥምን እንደ አንድ ሃይለኛ የጂሃድ መሳሪያ እየተጠቀመ ነው ያለው  ዘገባው፤የሽብር ቡድኑ የግለሰቦችን ቀልብ የሚስቡ አማላይ ግጥሞችን በማሰራጨት ሰፊ የፕሮፓጋንዳና የቅስቀሳ ስራ  እንደሚያከናውን አስታውቋል፡፡ ኦሳማ ቢን ላደን በ2000 ዓ.ም በተፈጸመ ጥፋትና በሌሎች የአልቃይዳ አንቅስቃሴዎችና አላማዎች  ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችን እንደጻፉ ያስታወሰው ዘገባው፣ ሌላ የቀድሞ የቡድኑ መሪ የጻፋቸው ስሜት  ቀስቃሽ ግጥሞችም፣ በቡድኑ ለሽብር ተመልምለው ሲሰለጥኑ የነበሩ ጂሃዲስቶችን ለጥቃት ለማነሳሳት በስፋት  ተሰራጭተው እንደነበር አመልክቷል፡፡

Read 2390 times