በበርሜል ከ37 ዶላር በታች ደርሷል
የአለም የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ካለፉት 11 አመታት ወዲህ እጅግ ከፍተኛው ሆኖ የተመዘገበውን የዋጋ ቅናሽ በማሳየት በበርሜል ከ37 ዶላር በታች መድረሱን የነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ድርጅት ኦፔክ አስታወቀ፡፡
ባለፈው አመት በበርሜል ከ110 ዶላር በላይ ይሸጥ የነበረው ነዳጅ፣ ከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ ሊያስመዘግብ የቻለው ከፍተኛ አቅርቦት በመኖሩና የአገራት የኢኮኖሚ እድገት እየተዳከመ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ የነዳጅ ፍላጎት እየቀነሰ በመምጣቱ ነው ሲል ኦፔክ ማስታወቁን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በነዳጅ ላይ የዋጋ ቅናሽ መፈጠሩ እንግሊዝን በመሳሰሉ አገራት ለተጠቃሚዎች በርካሽ ዋጋ ነዳጅ የማግኘት እድል መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ይሄም ሆኖ ግን ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየው የነዳጅ ዋጋው በአዲሱ አመት ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኦፔክ መግለጹን አስረድቷል፡፡
የአለም የህዝብ ቁጥር እና የኢኮኖሚ እድገት የሃይል ፍላጎትን እስከ 2040 በግማሽ ያህል ያሳድገዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጸው ኦፔክ፣ ከዚህ ጋር ተያይዞም የነዳጅ ፍላጎት ጭማሪ እንደሚያሳይ ግምቱን አስቀምጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል