Tuesday, 29 December 2015 07:48

በቦኮ ሃራም ሳቢያ ትምህርት ያቋረጡ 1 ሚ. ደርሰዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ቡድኑ ከ2 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶችን አዘግቷል

ጽንፈኛው ቡድን ቦኮ ሃራም በናይጀሪያ፣ ካሜሩን፣ ቻድና ኒጀር በሚያደርጋቸው የሽብር ተግባራት ሳቢያ ትምህርታቸውን ያቋረጡ ተማሪዎች ቁጥር 1 ሚሊዮን ያህል መድረሱን ዩኒሴፍ አስታወቀ፡፡
የሽብር ቡድኑ ከ2 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶችን አዘግቷል፣ በመቶዎች በሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች ላይም የሽብር ጥቃት፣ ዘረፋና በእሳት የማቃጠል ድርጊቶችን ፈጽሟል ያለው ተቋሙ፣ ቦርኖን በመሳሰሉ የናይጀሪያ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ስደተኞች መጠለያነት መቀየራቸውን ገልጧል፡፡
ቦኮ ሃራም የምዕራባውያንን አስተምህሮ አምርሮ ከመጥላቱ ጋር በተያያዘ፣ ትምህርት ቤቶችን ልዩ የጥቃት ኢላማው እንደሚያደርግ የጠቆመው ዘገባው፣ ባለፈው አመት ሚያዝያ ወር ላይም ከናይጀሪያዋ ቺቦክ ከተማ 200 በላይ የአዳሪ ትምህርት ቤት ልጃገረዶችን መጥለፉን አስታውሷል፡፡
ቡድኑ እንቅስቃሴውን ማድረግ ከጀመረ አንስቶ ባሉት ያለፉት ስድስት አመታት 17 ሺህ ያህል ዜጎችን መግደሉንና ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎችንም ከመኖሪያ ቦታቸው አፈናቅሎ ቤት አልባ ማድረጉን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1272 times