Saturday, 19 December 2015 11:07

የካናዳው ኩባንያ ለቻይናውያን ንጹህ አየር አሽጎ እየሸጠ ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

- አንድ ጠርሙስ ኦክስጂን 27.99 ዶላር ይሸጣል

በቻይና የአየር ብክለት እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያ ከተራሮች ላይ ተወስዶ በጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ለቻይናውያን እየሸጠ እንደሚገኝ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
በዚህ ወር መጀመሪያ የቻይና የአየር ብክለት መጠን ከፍተኛው ደረጃ ላይ መድረሱንና ለጤና ጎጂ መሆኑ ታምኖበት በመዲናዋ ቤጂንግ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉና የግንባታ ስራዎች እንዲቋረጡ መደረጉን ያስታወሰው ዘገባው፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያም ከሰሞኑ የታሸገ አየር ለቻይና ማቅረብ መጀመሩን ገልጧል፡፡
ኩባንያው ፕሪሚየም ኦክስጂን በሚል አሽጎ የሚሸጠው ንጹህ አየር በጠርሙስ 27.99 ዶላር እየተቸበቸበ ነው ያለው ዘገባው፣ የኩባንያው ተወካይም ገበያው እንደደራላቸውና ምርቱ በቻይና ገበያ ውስጥ ከፍተኛ ተፈላጊነት ሊያገኝ መቻሉን መናገራቸውን አስታውቋል፡፡
የኩባንያው ተወካይ ሃሪሰን ዋንግ እንዳሉት፤ ኩባንያው በመጀመሪያ ዙር ለቻይና ገበያ ያቀረበው 500 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ተሸጦ ያለቀ ሲሆን፣ ተጨማሪ 700 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየርም በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ቻይና ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 2033 times