Saturday, 19 December 2015 10:55

ኖርዌይ ዘንድሮም ለኑሮ የምትመች የአለማችን ቀዳሚ አገር ናት ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

- ላለፉት 12 አመታት የሚገዳደራትአልተገኘም
- ለኑሮ የማትመቸዋ የአለማችን የመጨረሻዋ አገር ኒጀር ናት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም በየአመቱ ይፋ በሚያደርገው ሂዩማን ዲቨሎፕመንት ኢንዴክስ ሪፖርት ውስጥ ለኑሮ ምቹ የሆኑ የአለማችን አገራት ዝርዝርን ላለፉት 11 አመታት በቀዳሚነትን ይዛ የዘለቀችው ኖርዌይ፣ ዘንድሮም በቀዳሚነት መቀመጧን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
አማካይ የህይወት ዘመን፣ ትምህርት፣ ገቢ እና የኑሮ ደረጃን በመስፈርትነት በማስቀመጥ የአለማችንን አገራት እየገመገመ ደረጃ የሚሰጠው ተቋሙ፤ ኖርዌይ በሁሉም መስፈርቶች ከፍተኛውን ውጤት በማስመዝገብ ዘንድሮም ለኑሮ ምቹዋ አገር ለመሆን መብቃቷን አስታውቋል፡፡
በኖርዌይ አማካይ የህይወት ዘመን 81.6 አመት ሲሆን ጠቅላላ አመታዊ ብሄራዊ የነፍስ ወከፍ ገቢዋም 64ሺህ 992 ዶላር መድረሱንና ይህም በተቋሙ ጥናት ከተካተቱት 188 ያህል የአለማችን አገራት በቀዳሚነት እንዳስቀመጣት  ዘገባው ገልጧል፡፡ ከኖርዌይ በመቀጠል እስከ አምስተኛ ደረጃን የያዙት የአለማችን አገራት አውስትራሊያ፣ ስዊዘርላንድ፣ ዴንማርክና ኒዘርላንድስ ናቸው ተብሏል፡፡
ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ አምስት የአለማችን አገራት የተባሉት ደግሞ ኒጀር፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኤርትራ፣ ቻድ እና ብሩንዲ ናቸው፡፡

Read 1369 times