Print this page
Saturday, 12 December 2015 11:56

በውሃና በሳሙና የሚታጠብ ሞባይል በገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ለ700 ጊዜያት ያህል ታጥቦ፣ አገልግሎቱን አላቋረጠም
    ኪዮሴራ የተባለው የጃፓን የሞባይል አምራች ኩባንያ በአለማችን የስማርት ፎን ታሪክ በአይነቱ የመጀመሪያው የሆነውን በውሃና በሳሙና መታጠብ የሚችል ዲንጎ ራፍሪ የተሰኘ አዲስ የሞባይል ቀፎ አምርቶ ትናንት በገበያ ላይ ማዋሉን ሪያሊቲ ቱዴይ ድረገጽ ዘገበ፡፡ ምንም እንኳን ሶኒ ኩባንያን የመሳሰሉ የሞባይል አምራቾች ከዚህ ቀደም ውሃን መቋቋም የሚችሉ ሞባይል ስልኮችን ቢያመርቱም፣ ሞባይሎቹ ሳሙና ከነካቸው የሚበላሹ ነበሩ ያለው ዘገባው፣ ኪዮሴራ ያመረተው አዲስ ሞባይል ግን የሳሙና አረፋ ውስጥ ተዘፍዝፎ ቢውል አይበላሽም ብሏል፡፡
“ይህንን በአይነቱ ልዩ የሆነ ሞባይል ስልክ ያመረቱት የኩባንያችን ተመራማሪዎች፣ የስልኩን ብቃት ለማረጋገጥ ከ700 ጊዜያት በላይ ያጠቡት ሲሆን አንዳችም ችግር ሳይፈጠርበት አገልግሎት መስጠት መቀጠሉን አረጋግጠዋል” ብለዋል የኩባንያው ቃል አቀባይ፡፡ 465 ዶላር የተተመነለት ይህ የሞባይል ስልክ፣ በተለይም ልጆች ለሚበዙባቸው ቤተሰቦች ታልሞ የተመረተ እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፣ ሞባይሉ ውሃና የሳሙና አረፋን መቋቋም የሚችል ሽፋን ያለው መሆኑንና፣ ስፒከሮቹን ጨምሮ የተገጠሙለት አካላት በሙሉ በፈሳሽ የማይበላሹ መሆናቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 3713 times
Administrator

Latest from Administrator