Saturday, 05 December 2015 09:29

አይሲስ ከ300 በላይ አሜሪካውያን የትዊተር አምባሳደሮች አሉት

Written by 
Rate this item
(4 votes)

    አይሲስ ትዊተር በተባለው ታዋቂ የማህበራዊ ድረ ገጽ አማካይነት የሽብር እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት የሚያግዝ የፕሮፓጋንዳ ስራ የሚሰሩና ለሽብር ቡድኑ አዳዲስ አባላትን የሚመለምሉ ከ300 በላይ አሜሪካውያን አምባሳደሮች እንዳሉትና አብዛኞቹም ሴቶች እንደሆኑ ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡
የጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የጽንፈኝነት ጥናት ፕሮግራም ተመራማሪዎች፣ በአሜሪካ የሚኖሩ የአይሲስን አላማ የሚያቀነቅኑ ግለሰቦች በተለይም ትዊተር በተባለው ማህበራዊ ድረገጽ አማካይነት የፕሮፓጋንዳና የምልመላ ስራቸውን እንደሚያከናውኑ የገለጹ ሲሆን ምንም እንኳን ትዊተር፣መሰል አካውንቶችን በተደጋጋሚ ቢዘጋም የተጠቃሚዎቹ ቁጥር ግን አልቀነሰም ብለዋል፡፡ ትዊተር ከአይሲስ ጋር ንክኪ አላቸው ብሎ የሚገምታቸውን አካውንቶች እየተከታተለ ቢዘጋም፣ ተጠቃሚዎቹ በሰዓታት እድሜ ውስጥ አዲስ አካውንቶችን በመክፈት፣ ከዚህ ቀደም የነበራቸውን ያህል የተከታይ ቁጥር እያገኙ ነው ብለዋል አጥኚዎቹ፡፡
ተጠቃሚዎቹ በዋናነት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ከሽብር ጋር በተያያዙ የተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩና የሽብር ቡድኖች በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጽሟቸውን የሽብር ጥቃቶችም ሲደግፉና ሲያደንቁ እንደተገኙ ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 2812 times