Saturday, 28 November 2015 14:34

የሰሜን ኮርያ ወንዶች ጸጉራቸውን ከ2 ሴ.ሜ እንዳያስረዝሙ ተከለከሉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

   ሰሜን ኮርያ የአገሪቱ ወንዶች ጸጉራቸውን ከ2 ሴንቲ ሜትር በላይ እንዳያሳድጉ የሚከለክል ትዕዛዝ ያስተላለፈች ሲሆን የመዲናዋ ባለስልጣናት ጸጉራቸውን ከዚህ በላይ ያሳደጉትን ዜጎች በቁጥጥር ስር እያዋሉ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በሚታወቁበት የጸጉር ስታይል አሳጥረው እንዲቆረጡ እያስገደዱ መሆኑ ተዘገበ፡፡
ዘ ቴሌግራፍ፣ ቾሱን ኢቦ የተባለው የደቡብ ኮርያ ጋዜጣ ሰሞኑን ያወጣውን ዘገባ ጠቅሶ እንዳለው፣ የመዲናዋ አስተዳደር የፒንግያንግ ነዋሪ የሆኑ ወንዶች ጸጉራቸውን በኪም ጆንግ ኡን ስታይል በመቆረጥ፣ለፕሬዚዳንቱ ያላቸውን ክብር እንዲያሳዩ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡
የከተማዋ ባለስልጣናት ያሰማሯቸው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ተቆጣጣሪዎች፣ መቀስ ይዘው በየቦታው እየተዘዋወሩ፣ረጃጅም ጸጉር ያላቸውን ወንዶች አሳጥረው ማስተካከል መጀመራቸውም ተነግሯል፡፡
የከተማዋ ሴቶችም ቢሆኑ የጸጉር አሰራራቸውን የፕሬዚዳንቱ ሚስት የሆኑት ቀዳማዊት እመቤት ሪ ሶል ጁ፣ በሚያዘወትሩት የጸጉር አሰራር መልክ እንዲያስተካክሉ ታዝዘዋል ብሏል ዘገባው፡፡

Read 4223 times