Saturday, 28 November 2015 14:20

“የሚበርድ ፀሐይ” የግጥም መድበል ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   መኖሪያቸውን ለንደን ባደረጉት ደራሲ ኤርሚያስ ሚካኤል (ሕርይቲ) የተፃፈው “የሚበርድ ፀሐይ” የተሰኘ የግጥም መድበል፤ ነገ ጠዋት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ትንሷ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መጽሐፉ በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው የተፃፉ 78 ግጥሞችን አካትቷል፡፡ በምረቃው ሥነሥርዓት ላይ ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ታዳሚያን በኮሜዲ ዝግጅቶች እንደሚዝናኑም የዝግጅቱ አስተባባሪ አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንት የፕሬስ ስራዎች ድርጅት ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡

Read 2305 times