Saturday, 14 November 2015 09:56

አሜሪካ የአልሻባብ መሪዎችን ለጠቆማት 27 ሚ. ዶላር ትሰጣለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    የአሜሪካ መንግስት በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰውን የሽብር ቡድን የአልሻባብን ስድስት መሪዎች የሚገኙበትን ስፍራ ለጠቆመው ሰው ወይም ተቋም፣ 27 ሚሊዮን ዶላር በዎሮታ መልክ እንደሚሰጥ ማስታወቁን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
አሜሪካ ባለፈው አመት በሰነዘረችበት የድሮን ጥቃት የገደለችውን አህመድ አብዲ ጎዳኔን በመተካት፣ ቡድኑን በዋና መሪነት በማንቀሳቀስ ላይ የሚገኘውን አቡ ኡባይዳህን በተመለከተ መረጃ ለሰጣት፣ ከፍተኛውን የ6 ሚሊዮን ዶላር ወሮታ እሰጣለሁ ማለቷን ዘገባው ገልጿል፡፡
በኬንያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በተከሰተውና 148 ሰዎች በሞቱበት የቡድኑ የሽብር ጥቃት ቁልፍ ሚና እንደተጫወተ የሚነገርለትን ማሃድ ካራቴ ወይም አብድራህማን ሞሃመድ ዋርሳሜ የተባለ የቡድኑ አመራር፣ የቡድኑ የምልመላና የስልጠና ሃላፊ የሆነውን ማሊም ዳኡድ፣ የፋይናንስ ጉዳዮች ሃላፊውን ሃሰን አፍጎዬን፣ በአፍሪካ ቱሪስቶች ላይ በተሰነዘሩ የቡድኑ ጥቃቶች ላይ የተሳተፈውን ማሊም ሳልማንን እንዲሁም በኬንያ አዳዲስ የቡድኑ አባላትን በመመልመል ተሳትፏል ያለችውን አህመድ ኢማን አሊን በተመለከተ መረጃ ለሚሰጣት በድምሩ 27 ሚሊዮን ዶላር እሰጣለሁ ብላለች አሜሪካ፡፡

Read 1906 times