Saturday, 14 November 2015 09:07

የቻይናው ኩባንያ አሊባባ የዓለማችንን የዕለታዊ ሽያጭ ክብረወሰን ሰበረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    አሊባባ የተባለው የቻይና የኢንተርኔት ንግድ ኩባንያ ባለፈው ረቡዕ በተከናወነው ሲንግልስዴይ የተባለ አመታዊ ልዩ የሽያጭ ፌስቲቫል
ባስመዘገበው ሽያጭ፣ በራሱ ተይዞ የቆየውን የዓለማችን የኢንተርኔት ዕለታዊ ሽያጭ ክብረወሰን ያሻሻለ ሲሆን አጠቃላይ ሽያጩ ከ13.8
ቢሊዮን ዶላር በላይ ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመት ኤንቢሲ ኒውስ ዘገበ፡፡
ኩባንያው ረቡዕ ዕለት በተከናወነው “የሲንግልስ ዴይ” የሽያጭ ፌስቲቫል ላይ በስምንት ደቂቃ
ውስጥ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስመዝገቡንና ባለፈው አመት ያገኘውን የ9.3 ቢሊዮን ዶላርየዕለት ሽያጭ ገቢ ለማግኘት
የወሰደበት ጊዜ አምና ከነበረው በግማሽ ያነሰ መሆኑንም ዘገባው ጠቁሟል፡ ፡ኩባንያው በዘንድሮው የ “ሲንግልስ ዴይ” አለማቀፍ
ልዩ የሽያጭ ፌስቲቫል ላይ፣ ከ6 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ምርቶችን ለሽያጭ ማቅረቡንና በዕለቱም በአንድ ደቂቃ ከ120 ሺህ በላይ የግዢ
ጥያቄዎችንና 60 ሺህ ያህል ክፍያዎችን መቀበል የቻለበት ደረጃላይ መድረሱን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ሽያጩ በይፋ በተከፈተ በአንድ ሰዓት ጊዜውስጥ በሞባይል አማካይነት ብቻ 27 ሚሊዮን ግብይቶችን መፈጸሙን ያስተዋወቀው
ኩባንያው፤
በዕለቱ የሸጣቸውን የኤሌክትሮኒክስና የመዋቢያ
ዕቃዎች ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦችን በ1.7 ሚሊዮን
መልዕክተኞች፣ በ400 ሺህ መኪኖችና በ200
አውሮፕላኖች ለገዢዎች እንደሚያደርስም አክሎገልጿል፡፡

Read 3021 times