Saturday, 31 October 2015 08:42

ቻይናውያን ሁለት ልጆች መውለድ ሊፈቀድላቸው ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ለ35 አመታት የዘለቀው የ1 ልጅ ብቻ ፖሊሲ፣
ከ400 ሚ. በላይ ወሊዶችን አስቀርቷ
    ቻይና ዜጎቿ አንድ ልጅ ብቻ እንዲወልዱ የጣለችውንና ከ35 አመታት በላይ የዘለቀውን አስገዳጅ የስነህዝብ ፖሊሲ በማሻሻል፣ ሁለት ልጆችን መውለድ እንደሚችሉ የሚፈቅድ አዲስ ህግ ልታወጣ መወሰኗን ከትናንት በስቲያ ማስታወቋን ቢቢሲ ዘገበ፡፡የአገሪቱን የወሊድ መጠን ለመቀነስና የህዝብ ቁጥር ዕድገቱን ለመግታት ታስቦ የተቀረጸው “የአንድ
ልጅ ብቻ” ውለዱ ብሄራዊ ማዕቀብ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረበት እ.ኤ.አ ከ1979 ጀምሮ ባሉት
አመታት፣ በአገሪቱ ሊከሰቱ ይችሉ የነበሩ 400 ሚሊዮን ያህል ወሊዶች  መምከናቸውን ዘገባው
ጠቁሟል፡፡በአገሪቱ በእድሜ የገፉ ሰዎች ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱ፣ ቻይና ተተኪ ትውልድ እንዳታጣ
ስጋት መፍጠሩን ተከትሎ፣ መንግስት የወሊድ ገደቡን እንዲያሻሽልና ዜጎች ተጨማሪ አንድ ልጅ
መውለድ እንደሚችሉ ለመፍቀድ እንዳነሳሳው ተገልጧል፡፡አንድ ልጅ ብቻ ውለዱ የሚለውን ህግ ጥሰው ሌላ ልጅ ጸንሰው የተገኙ ቻይናውያን ሴቶች፤ ጽንሱን እንዲያጨናግፉ ይገደዱ እንደነበር እንዲሁም ከስራቸው ይፈናቀሉና የተለያዩ ቅጣቶች ይጣሉባቸው እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1221 times