Print this page
Saturday, 24 October 2015 09:49

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በሞተር ብልሽት ለማረፍ ተገደደ

Written by 
Rate this item
(13 votes)

ወደ ጋምቤላ ሲጓዝ የነበረ ሌላ አውሮፕላንም ጎማው በመውለቁ ተመልሶ ማረፉ ተነግሯል

ትላንት ማለዳ ከአየርላንድ ደብሊን አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ወደ ዋሽንግተን በመብረር ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET500 ቦይንግ 787-800 አውሮፕላን በግራ ሞተሩ ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ጉዞውን አቋርጦ ወደ መነሻው መመለሱንና ጉዳት ሳይደርስ በሰላም ማረፉን አየርመንገዱ አስታወቀ፡፡
የቴክኒክ ብልሽቱን ሰበብ ለማወቅ በአየርመንገዱ የቴክኒክ ባለሙያዎችና በጂኢ ኢንጂነርስ ባለሞያዎች ትብብር ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝም የጠቆመው አየር መንገዱ፤ አውሮፕላኑ ተቀይሮ ጉዞው ወደ ዋሽንግተን መቀጠሉን ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ጉዞው በመስተጓጎሉ ሳቢያ በመንገደኞች ላይ ለተፈጠረው መንገላታትም ይቅርታ ጠይቋል፡፡
አይሪሽ ሚረር በበኩሉ፤ አውሮፕላኑ ከደብሊን አውሮፕላን ጣቢያ ተነስቶ ከአንድ ሰዓት ተኩል በላይ ከተጓዘ በኋላ በገጠመው የቴክኒክ ብልሽት ሳቢያ አንደኛው ሞተሩ ጠፍቷል መባሉን ጠቁሞ፣ ከ300 በላይ መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ እንደነበርም ትናንት ዘግቧል፡፡
በተያያዘ ዜና፤ ባለፈው ሰኞ በበረራ ቁጥር ET -150 ከቦሌ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ተነስቶ ወደ ጋምቤላ በመብረር ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦምባርዲየር Q-400 አውሮፕላን፤ አንደኛው ጎማው ወልቆ በመውደቁ ሳቢያ ተመልሶ ለማረፍ መገደዱን ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡
በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት 55 መንገደኞችና 4 የበረራ ቡድን አባላት ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰባቸውም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡  

Read 6347 times
Administrator

Latest from Administrator