Saturday, 24 October 2015 08:39

ፌስቡክ ተጠቃሚዎቹን ከመንግስታት ጥቃት ለመታደግ አስቧል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ማስጠንቀቂያ የደረሰው ተጠቃሚ፣
ፈጣን እርምጃ መውሰድ አለበት
ታዋቂው የማህበራዊ ድረ-ገጽ ፌስቡክ፣ በአገራት መንግስታት የሚደገፉ የድረገጽ የስለላ ጥቃቶች ለሚሰነዘሩባቸው ተጠቃሚዎቹ መረጃ በመስጠት፣ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያስጠነቅቅበትን አዲስ አሰራር ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን ኒውስ የተባለ ድረ ገጽ ዘገበ፡፡ፌስቡክ አንድ ተጠቃሚው በመንግስታት የሚደገፍ የስለላ ጥቃት እየተፈጸመበት እንደሚገኝ የሚያመለክቱ ተጨባጭ ማስረጃዎችን ሲያገኝ፣ ‘Please Secure Your Accounts Now’ የሚል ርዕስ ያለውና የፌስቡክና የሌሎች አካውንቶቹ የጥቃት ሰለባ ሳይሆኑ እንዳልቀሩ የሚገልጽ የማስጠንቀቂያ መልዕክት በአፋጣኝ ለተጠቃሚው እንደሚልክ አስታውቋል፡፡ተጠቃሚው መልዕክቱ እንደደረሰው የይለፍ ቃሉን ከመቀየር ባለፈ፣ የሚጠቀምበትን ሞባይል
ወይም የኮምፒውተር ሲስተም በአዲስ መልኩ መስራት ወይም መቀየር ይጠበቅበታል  ሲልም አስጠንቅቋል፡፡አዲሱ የማስጠንቀቂያ አሰራር ከለላ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ
የጠቆመው ፌስቡክ፣ በማህበራዊ ድረገጹ ተጠቃሚዎች ላይ የሚቃጡ ጥቃቶችን የመከላከልና የመለየት አቅሙን በማሳደጉ እንደሚገፋበትም ጠቁሟል፡፡ በመንግስታት ከሚደገፉ ከፍተኛ የድረገጽ ጥቃቶች መካከል፣ ባለፈው አመት የሰሜን ኮርያ መንግስት ሶኒ ኢንተርቴንመንት በተባለው ታዋቂ ኩባንያ ላይ የሰነዘረው ጥቃት ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1943 times