Saturday, 10 October 2015 16:03

የጉዞ ማስታወሻ (ካለፈው የቀጠለ)

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ደብረዘይት፣ አዴ ወረዳ እና ሻሸመኔ የብሾፍቱ ማህበራዊ ተጠያቂነት ማጠቃለያ
ባለፈው የደብረዘይት/ብሾፍቱ ጉዞዬን ጀምሬ ነበር፡፡ ላጠቃልለውና ወደ አጄ ጉዞዬ እቀጥላለሁ፡፡
ስለናንተ ጉዳይ (ስለማህበራዊ ተጠያቂነት) የጋዜጣችን አንባቢ ያውቅ ዘንድ ቀለል አድርጌ ልጽፍ ነው፡፡
አገልግሎት ሰጪዎችና አገልግሎት ተቀባዮች ናቸው መልስ የሰጡኝ፡፡ ማህበራዊ ተጠያቂነት በብሾፍቱ ምን ይመስል ነበር? ከዚያስ በኋላ ውጤቱ ምን ሆነ?
የት/ቤትን ችግሮች በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም
የክፍል ጥበቶች ነበሩ፤ተሠርተው በነፃነት ይማራሉ
መፀዳጃ ቤቶች አዲስ መሠራት ብቻ ሳይሆን የወንድና የሴት ተብለው ተከፍለው እየተገለገሉባቸው ነው፡፡
ሜዳው አፈር ነበረ፤ አሸዋ ተደፍቶበታል፡
በአንድ ጠረጴዛ ላይ ለ5 ለ6 የሚማሩት አሁን ለ3 እንዲማሩ ተደርጓል
አንድ መጽሐፍ ለ3 ለ2 ያልነበረውን፣ አሁን መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ እንዲያገኝ ጥረት ተደርጓል - ይህ የሆነው በህብረተሰቡ ድጋፍ ሲሆን፤ ይህም የእየሩሳሌም ህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት (ጄክዶ) አካባቢውን ለቅቆ ቢሄድ ህብረተሰቡ በዘላቂነት ሊረከብ እንደሚችል ይጠቁማል፡፡
ኤችአይቪ ፖዘቲቭ የሆኑ ስለመድሃኒቱ አጠቃቀም በጥንካሬያቸው የሚያሳምኑ የሳክ አባላት ይፋ ገለፃ እንዲያደርጉ ተደርጓል (ግን ይቀረዋል)
በውሃ በኩል አራት ችግርተኛ ቀበሌ ተለይቶ ተመርጦ ነው መፍትሔ ፍለጋ የተገባው! ት/ቤቶችም እንደዚያው!
ከአራቱ ቀበሌዎች ሁለት ሁለት መቶ ሰዎች እንዲሳተፉ ነው የተደረገው!
የመንግስት ስታንዳርድን መርምረዋል፡፡ እንዲጣጣሙ ለማድረግ ስኮር - ካርድ የምትባል መመዝገቢያ አለች፡፡ ውጤት ከ5 ይታረማል፡፡ የሁሉም ቀበሌ ስዕል ይገኛል፤ ለምሳሌ ካራ ሁራ 1.5 ሚሊዮን ብር ተመድቦ፣ 4 ባለ 8 መማሪያ ክፍል ሁለት ብሎኮች ተሠርቷል፡፡ ስታንዳርድ ጠረጴዛ ቀርቦልናል፡፡ (የሽንት ቤት ስታንዳርድም በቪዲዮ በተቀረፀው መሠረት መፍትሔ አገኘን - በህብረተሰቡና በሊንክ ኢትዮጵያ) እንደችግር የማህበረሰባዊ ተጠያቂነት ግንዛቤ አልነበረም፡፡ ችግሩን አምቆ ይይዝ ነበር፡፡
ለት/ቤቱ አባላት ብቻ ሳይሆን ለመንግሥትም ጠቀሜታ ያለው ነገር ተካሂዷል፡፡ የየክፍሉን ችግር ሁለቱም ወገኖች ተማምነው ለውጥ ስላዩበት! ተማሪዎች ረባሾችን ያጋልጣሉ! የመማር ማስተማር ሂደት በግልጽ የሚያምኑበት ሆኗል፡፡ ተማሪዎች የፈለጉትን ይጠይቃሉ!
ህዝብ አገልግሎት ሰጪዎችን ለሚጠይቅበት የካራ ሆራ ት/ቤት ምሳሌ ነው፡፡
Citizens report card እና የህብረተሰቡ ሃሳብ መስጫ ካርድ ተጠቅመዋል፡፡ መሞራረድ በመሟገት ጠቅሞናል፡፡
በ150 ብር የተሠራ ፕሮጄክት ነበር፤ በዐይናችን ሄደን አይተናል፡፡ ውሃ ልማት አይደለም፤ እኛ ነን ተሟጋቾች - ቴክኒካል ጉዳይ፣ የጥራት ጉዳይ፣ የኮንስትራክተሮችና የዕቃው ጥራት፣---- ሳቢያ እንዳለ ፓምፑ 400 ሜትር ሰመጠ፡፡ ሌላ ጄኔሬተር ተገዝቷል፡፡ ችግር along the line ነው አልተፈታም፡፡ ማህበራዊ ተጠያቂነት አጋዥ ነው፤ብቻችንን ወደላይ ስንጮህ አጋር አላገኘንምና! ትክክለኛ ኤክስፐርት እንደሌለ ነው የሚታየው! የክትትል ጥራት ማነስ!
የፍሳሽ መኪና ዕጥረት ነበር በከፍተኛ ወጪ ተገዝቷል!
በወር አንድ ጊዜ በህብረተሰቡ የጽዳት ዘመቻ ይካሄዳል
በእኛና በት/ቢሮ መካከል ትልቅ መቀራረብ አለ!
የህዝቡ አማካሪ ምክር ቤት ፀሐፊ እንዳሉት - 1ኛና ሁለተኛ ፌዝ አባል - “የመንግስት የ5 ዓመት ዕቅድ እንደስታንዳርድ ተቆጥሯል፤ በግሩፕ አስበን ያልተሳኩትን እንደ ችግር ወስደን ነው፡፡ ከንቲባው ቃል ገቡ - ዕቅድና በጀት ተፈቀደ - የገንዳ ማጠራቀሚያና የቆሻሻ ማንሻ መኪና ዕጥፍ ሆኑ!
ፊት የተገዛው ፓምፕ ለሙቅ አይሆንም ነበር፤ ህዝቡ አልረካንም ብሏል
በት/ቤት ግቢ ያሉ ቤቶች ማካካሻ ቦታና ቤት ተሠርቶላቸው ለቀዋል! ኮንዶምኒየም የገቡ አሉ!
ለመላው ኢትዮጵያ ምሳሌ እየሆነ ነው፤ ከሶማሊያና ከኬንያ ጭምር መጥተው ጐብኝተዋል! መተሃራ ምንጃር አካባቢ ልምድ ከካራ ሆራ ት/ቤት አግኝተናል ብለዋል ከዝቅተኛ ወደ ከፍተኛ ስለሄደ!
አንገብጋቢው ነገር ላይ ስላለሁ ሁሌ እንዳነባሁ ነው፤ ውሃ የለም፤ ወልደው መታጠቢያ፣ ለአስከሬን ማጠቢያ እንኳን! (ቀበሌ 08)
3 ቀን ብቻ የመጠጥ ውሃ አገኘን! ደሞ የፈላ ውሃ ብቻ ለቀቁብን ይላሉ፤ባልቴቷ ተወካይ! ይሁን አቀዝቅዘን እንጠጣ አልን፤ከ2 ቀን በኋላ ቀጥ አለ!
ወዴት እንሂድ፤ ከዚህ በላይ አቤት የት አለ፤ ከንቲባው በተቀመጡበት ተናገርን!
“የጠገበ ሰው የተራበን ሰው ነገር አያቅም! በ6 ወር ዝናብ ከዘነበ ድንገት አጠራቅመን ነው የምንታጠበው፤እነሱ ግን ፀድተው ይወጣሉ! አብሲት የምንጥለው የምናቦካው በዝናብ ውሃ ነው፤ ለአሁን ክረምት!
ግን አሁን በቦቲ ይመጣል፤ ለዛ ሁሉ ህዝብ እንዴት ያዳርሳል? እሱም ህዝቡ ቀይ አሸዋ አልብሶ ነው ----- መናገሩን በውሃ ጉዳይ ላይ አቁሜያለሁ - ጉድጓድ ውሃ ገባ አሉ፣ ሞተር ገብቷል ውስጡ ተባለ - ሄደን ውሃ ልማት መጠየቃችን አልቀረም - እኮ! ከአሜሪካን አገር ሰው አምጥተን አሉ፤ ትልቁ አገር አሜሪካን ነው አሉ እንግዲህ አቅቶት ሄደ (ሳቅ) ሌላ ማን ሊያወጣው ነው ታዲያ?
እኔ መሀይም ነኝ አላቅም፤ አፍርሰውት ቢያወጡት ሰብረው! አልወጣም አይል፡፡
ህዝቡ ከማልቀስ ውጪ አደለም፤ አንድ በርሜል 100 ብር ነው!
ትምህርትስ አልተሻሻለም?
ትምርቱ ግን ጥሩ ነው ፤ግን ሲማር ውሃ ያስፈልገዋላ መቼም!
ከላይ የተጠቀሰው የድፍን ብሾፍቱ ችግር አይደለም፤ መንግሥት ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት ነው እንጂ!
ሰው ራሱ ተጠያቂ መሆኑን አውቋል፤ ችግሩንም ይፋ መናገር እንዳለበት ተገንዝቧል፤ ትልቅ ለውጥ አለ!
አየር ኃይልና አሻም አፍሪካ አግዘውናል
091307 ቀበሌ የበጀት ተወካይ እህማልድ ታላቅ አስተዋጽኦ ትልቅ ድርጅት ነው - የራሳችንን ችግር በራሳችን እንድናወጣ - እሾክን በሾክ! አንድ ዐይናችን ነው! 26 ሴክተር መ/ቤቶች ከነ ከንቲባው ከነአባላቱ ጭምር ከጄክዶ ጋር ተሰብስበው፤ ተወያይተው የማተ ኮሚቴ እንደ አገር ብልጽግና ታዳጊ ሆኖ ከሥር እየተመካከረ በቡና፣ በዕድር፣ በቀብር፣ በውይይት ላይ በቀበሌ ሰብሳቢዎች ላይ - ነገሬ ብሎ እንዲያስብ አድርጓል - በከተማ ልማት ዕቅድም ህዝቡ ከታች እንዲመክርበት በጐጥ አድርጓል - እኔ አውቅልሃለሁ እንዲቀር ጥሯል፡፡
እንደ ችግሩና እንደተጠቃሚው ብዛት እንዲሆን አድርጓል
በጀት ይለጠፋል፤ ህዝቡ ሃሳብ እንዲሰጥ
50 50 በጀት ከመንግሥት ጋር እንዲሠራ ደረጃ ላይ ደርሷል
የተራ ሆራ የልጅ ሃ/ማ ነው
   ለግል መኖሪያ ያሠሩት ነው!
ግልጋሎት ሰጪው የመንግሥት አካል የህዝቡን ጥያቄ እየተቀበለ ነው! ትልቁ ነገር ለመላው ኢትዮጵያ የሚሆን እየተፈጠረ ነው!
ባቦ ጋያ ህፃናት መዋያ ተጀምሯል፤ እኛ ራሳችን በጐ ተፅዕኖ መፍጠር አለብን፤ መጨቃጨቅ መካሰስ መቃወም ሳይሆን! ጀምረነዋል - በትዕግሥት!!
መጽሐፍ ስቶር ይገባል፤ይሠራጭ አይሠራጭ የሚከታተል የለም! አሁን ያ ተለውጧል!
የማህ/ተጠዋና ሥልጣን የማቀጣጠል ሥራ ነው!
በኤችአይቪ ዙሪያ ቤት እስከመስራትና እስከቁጠባ ተሠማርቷል - ጄክዶ!
የአካል ጉዳተኞች ላይ ትኩረት አድርጐ እርዳታ ያጠናክር! የመንግስት ባጀት ሲመደብ
ወጣት ላይ ይሠራ ፤ለመተካካት!
አገልግሎት ሰጪው ቆልፎ እንዳይይዝ ከፖለቲካ ጋር አይቆላለፍ awareness ይሰጥ! መልካም አስተዳደር ይታሰብበት!
***
ቀጥሎ የተጓዝኩት ወደ ሻሸመኔ ሲሆን ከዚያ 30 ኪ.ሜ ገደማ ወደቀኝ ተገብቶ አጄ ወረዳ ይደረሳል፡፡
የአጄ የማህበራዊ ተጠያቂነት ኮሚቴ መርምሮ አዎንታዊ ውጤት ማምጣቱን ሲናገር፣ የሳክ የትምህርት ኮሚቴ ሊመንበር አቶ መርዕድ ዋናው ጉዳይ አገልግሎት ሰጪውና አገልግሎት ተቀባይ የግንዛቤ ለውጥ ማምጣታቸው ነው፤ የችግሩን ባለቤት ማስገኘትና ለውጥ ማስከተል ሲሆን በዚህ ረገድ ተጨባጭ ውጤት ታይቷል፤ ድፍረት ታይቷል፤ ትምህርት፣ ውሃና ንፅህና ላይ ነው ውጤቱ የተመዘገበው፡፡ ሽንት ቤት ለሌለው ሽንት ቤት ተሠርቷል፡፡ ህዝብ ይገባኛል ያለውን መንግሥት ይገባል ብሎ ፈጽሟል፡፡ ይጠፋ የነበረውም ውሃ መጥፋት የለበትም ተብሎ የኦሮሚያ የውሃ መ/ቤት፣ ወደ አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ትልቅ ጄኔሬተር ተገዝቶ፣ የውሃም የመብራትም ችግር እንዳይኖር ሆኗል፡፡ ሻወር አልነበረም ኖረ፡፡ ልብስ ማጠቢያ ኖረ፡፡ ሃሳብ በዐይን ተተግብሮ ታየ፡፡ አቶ አማን ደግሞ ስለ ገጽ ለገጽ ምን ዕውነታ አለ ብያቸው፣ ዋናው ነገር አገልግሎት ሰጪና ተቀባይ አጠገብ ላጠገብ ተቀምጠው በድፍረት መናገራችን ነው! ብለዋል፡፡ የዛሬ ሁለት ዓመት በተወያየነው መሠረት፤ በግለሰብ ደረጃ ሽንት ቤት የሌለው እንዲኖረው፣ በማህበረሰብ ደረጃም የህዝብ ሽንት ቤት እንዲሠራ ተደርጓል፡፡ ሥራ ባግባቡ ባለቤት አግኝቶ፣ መሬት ላይ የሚታይ ለውጥ ተገኝቷል፡፡
እንዳገር ሽማግሌ ይሄን አይቻለሁ፡፡ እጅ መታጠቢያም ተሠርቷል፡፡ በጽዳት በኩልም ደረቅ ቆሻሻ አንድ ቦታ ተሰብስቦ እንዲቃጠል፣ እርጥቡ ጉድጓድ እንዲገባ ተደርጓል፡፡ በውሃ በኩል ቦኖ ተደርጓል፡፡ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና ህብረተሰብ ተገኝተዋል፡፡ የሴክተር ቢሮዎችም የልምድ ልውውጥም ተካሂዷል፡፡ የሴቶች ኃላፊም፣ ሴቶች እንዲሳተፉ በጽዳቱም፣ በውሃውም በትምህርቱም ተደርጓል፡፡
ያለው ችግር የውሃው ኃይል ማጣት ነው፡፡ ጫካው ተመናምኗል፡፡ ለመተካት እየተሞከረ ነው፡፡ ግንዛቤ መጨበጥ፣ ችግር ማጤን፣ ማቀድ መበጀትና ውጤት ማምጣት ነው ተግባራዊ ሂደቱ! “ራሳችሁ ላይ ያለው ለውጥ ምንድን ነው? ብዬ ለጠየኳቸውም፤“ስልጠና ማግኘታችንና ችግርን በድፍረት ማንም ፊት መናገር መቻላችንን ተረድተናል፣ በፊት እንፈራ ነበር” ብለዋል አባላቱ! የስዊድን ልማት ድርጅትና ዓለም ባንክ ከእየሩሳሌም ድርጅት ጋር የሠሩ ሲሆን፤ ከመጠየቅ መጠየቅ (ጠ ይጠብቃል) እንደሚከብድም አስምረውበታል፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ግብርና ቢሮ አመራሁ፤ እዚያው ያለውን ስብሰባ ለማየት ነው! 

Read 2298 times