“መርካቶ ሰፈሬ” በሚለው የመጀመሪያ አልበሙ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምፃዊው አብዱ ኪያር፤ “ጥቁር አንበሳ” በሚል ስያሜ አራትኛ አልበሙን ሰሞኑን ለአድማጭ አድርሷል፡፡ የአልበሙን መጠሪያ ጨምሮ 11 ዘፈኖች የተካተቱበት የሙዚቃ አልበሙ፤ በአሸብር ማሞ የተቀናበረ ሲሆን ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ዜማ ስቱዲዮ ውስጥ እንደታተመ በአልበሙ ሽፋን ላይ ተገልጿል፡፡ በግጥምና በዜማ ድምፃዊውን ጨምሮ በርካታ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ታዋቂው ሙዚቀኛ ፈለቀ ሀይሉ በሳክስፎን አጅቦታል፡፡ ዘፈኖቹ በፍቅር፣ በአንድነት፣ በትውስታና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚያጠነጥኑም ለማወቅ ተችሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና