Saturday, 19 September 2015 09:35

ጨረቃ እየተኮማተረች ነው ተባለ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

    ከስድስት አመታት በላይ በጠፈር ላይ የቆየቺው ሉናር ሪኮኔሳንስ ኦርቢተር የተባለች የናሳ የጠፈር መንኮራኩር፣ ይሄን አጀብ የሚያሰኝ ዜና ይፋ አድርጋለች - ጨረቃ እያደር መጠኗ እያነሰና እየተኮማተረች መሄዷን ቀጥላለች፡፡
የጠፈር መንኮራኩሯ በተገጠመላት የረቀቀ ካሜራ ያነሳቻቸው ፎቶግራፎች፣ የጨረቃ መጠን ከዚህ በፊት ከነበረው እያነሰ መምጣቱን አመላክተዋል ሲል የዘገበው ሮይተርስ ነው፡፡
የጨረቃን ሶስት አራተኛ ክፍል መሸፈን በቻለው በዚህ ካሜራ የተነሱት ጥራት ያላቸው ፎቶግራፎች፣ በጨረቃ ላይ ከ3ሺህ በላይ ሰፋፊ ስርጉድ ስፍራዎች እንዳሉ የጠቆሙ ሲሆን ከአምስት አመታት በፊት የተነሱ ፎቶግራፎች ግን፣ በጨረቃ ላይ የነበሩት ስርጉድ ስፍራዎች 81 ብቻ እንደነበሩና የቁጥራቸው መብዛት ከጨረቃ መጠን እየቀነሰ መምጣት ጋር የተያያዘ ነው መባሉን ዘገባው አስታውቋል፡፡
የናሳ የጠፈር ተመራማሪዎች የጨረቃ መጠን እያነሰ የመጣው ከመሬት  ስበት ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ተጽዕኖ ነው ማለታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በራሷ በጨረቃ ውስጥ የሚታዩ የሙቀት መጠን ለውጦችም ለመጠኗ መቀነስ አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ መናገራቸውን አክሎ ገልጧል፡፡

Read 7429 times