ለአራት ቀናት የሚቆይ የኮንስትራክሽን እና አርኪቴክቸር አውደ ርእይ በመጪው ሐሙስ በኤግዚቢሽን ማዕከል ይከፈታል፡፡ የአውደ ርእዩ አዘጋጅ ስፔሲፋይ ካምፓኒ እንዳለው፤ በአውደ ርእዩ የውጭ ሀገር እና የሀገር ውስጥ የኮንስትራክሽን እቃዎች የሚቀርቡ ሲሆን በኢትዮጵያ አርኪቴክቸር ዙርያ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕንፃ ኮሌጅ እና ከኢትዮጵያ አርኪቴክቶች ማህበር የሚገኙ ባለሙያዎች ትምህርታዊ ገለፃ ያደርጋሉ፡፡