Monday, 31 August 2015 10:29

የየአገሩ ምሳሌያዊ አባባል

Written by 
Rate this item
(11 votes)

ስንፍና የኃጢያቶች ሁሉ ሥር ነው፡፡
   የግሪካውያን አባባል
እርቃኑን የተወለደ መልበስ ያሳፍረዋል፡፡
   የግሪካውያን አባባል
ወይ በጊዜ አግባ ወይ በጊዜ መንኩስ፡፡
  የግሪካውያን አባባል
በወይን ጠጅ ውስጥ እውነት አለች፡፡
  የሮማውያን አባባል
እናትና ልጅ ሲጣሉ፣ ሞኝ እውነት ይመስለዋል፡፡
  የአፍጋኒስታውያን አባባል
ድመቶች አይጥ የሚይዙት እግዚአብሔርን ለማስደሰት ብለው አይደለም፡፡
  የአፍጋኒስታውያን አባባል
ሞት ሲመጣ ጥሩንባ አይነፋም፡፡
  የኮንጎዎች አባባል
ስለ እሳት ማውራት ድስቱን አያበስለውም፡፡
  የአፍሪካ አሜሪካውያን አባባል
በእናቱ ጀርባ ላይ የተቀመጠ ህፃን የመንገዱን ርዝመት አያውቀውም፡፡
  የአፍሪካውያን አባባል
ቢራቢሮ መብረር ስለቻለች ብቻ ወፍ ነኝ ብላ ታስባለች፡፡
  የአፍሪካውያን አባባል
እስስት ቀለሟን እንጂ ቆዳዋን ፈፅሞ አትቀይርም፡፡
  የአፍሪካውያን አባባል
ቢላ ባለቤቱን አይለይም፡፡
  የአፍሪካውያን አባባል
የክፋትን ዘር በጊዜ ካላጠፋኸው አንተኑ ያጠፋሃል፡፡
  የቻይናውያን አባባል
ባሏ ከሞተ ሴት ጋር ግንኙነት ከመጀመርህ በፊት፣ ባሏን የገደለው ምን እንደሆነ መጠየቅ አለብህ፡፡
  የአፍሪካውያን አባባል

Read 3925 times