Monday, 31 August 2015 10:24

“አዲስ ዓይኖች” በዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫሎች እንዲታይ ተመረጠ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በወጣቷ የፊልም ባለሙያ ሕይወት አድማሱ የተሰራው “አዲስ ዓይኖች” የተሰኘው አጭር ፊልም በዓለም አቀፎቹ የቬነስና ቶሮንቶ ፊልም ፌስቲቫሎች ላይ እንዲታይ መመረጡ ተገለፀ፡፡
ፊልሙ አንዲት የ13 ዓመት ሴት ልጅ የሚጋጥማትን አካላዊና የስሜት ዕድገት ለውጥ ተከትሎ ከማህበረሰቡ ጋር የምትፈጥረውን ግጭት የሚያሳይ ነው ተብሏል፡፡
የፊልሙ ፀሐፊና ዳይሬክተር ህይወት አድማሱ፤ በመላው ዓለም ካሉ 10 ባለተሰጥኦ ወጣት የፊልም ሰሪዎች አንዷ ሆና በቶሮንቶው የፊልም ፌስቲቫል ለሚካሄድ ልዩ ፕሮግራም በመመረጥ ከአፍሪካ ብቸኛዋ እንደሆነች ገልፃለች፡፡
“አዲስ ዓይኖች” በእንግሊዝና በፈረንሳይ የፊልም ኩባንያዎች ፕሮዱዩስ እንደተደረገ ወጣቷ ተናግራለች፡፡
ህይወት በኤሌክትሪክና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ያገኘች ሲሆን በብሉናይል የፊልምና የቴሌቪዥን አካዳሚ ገብታም የፊልም ጥበብን ተምራለች፡፡ ወጣቷ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የፊልም ዎርክሾፕና ስልጠናም ላይ መካፈሏንም ጠቁማለች፡፡

Read 1612 times