Saturday, 04 February 2012 12:29

የአኬሽያ ዓለም አቀፍ የጃዝና ሙዚቃ ፌስቲቫል ተጀመረ “ሕይወት እዚህ ቦታ” ዛሬ ይቀርባል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(0 votes)

ሃያ ሰባት የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቡድኖች እና ሌሎች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ባለሙያዎች የሚሳተፉበት አኬሽያ የጃዝና የዓለምአቀፍ ሙዚቃ ፌስቲቫል ተጀመረ፡፡ ዝግጅቱ ትናንትና ከትናንት ወዲያ በጃዝ አምባ  እና በፈንድቃ የተጀመረ ሲሆን ዛሬ በትሮፒካል ጋርደን ይጀመራል፡፡ አሜሪካ፣ ስፔን፣ ኔዘርላንድ፣ ሊቷንያ እና ሌሎች ሀገሮች የመጡ ባለሙያዎች ከሚያቀርቡት የሙዚቃ ዝግጅትሌላየፓናልውይይትእንደሚኖርምታውቋል፡፡ በተጨማሪ ከ27 በላይ ዝግጅቶች እንደሚኖሩ የፌስቲቫሉ ተባባሪ መስራችና አዘጋጅ አርቲስት ግሩም መዝሙር ለዝግጅት ክፍላችን ተናግሯል፡፡

በዚሁ መሠረት ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊ ሙዚቀኛ ነገ ከቀኑ 11፡30 በጃዝ ክለብ አብሮት ከመጣው ቡድን ጋር ሥራዎቹን የሚያቀርብ ሲሆን ረቡዕ ምሽት በአሜሪካ ኤምባሲ “Music As a Business” የሚል የክብ ጠረጴዛ ውይይትም ይካሄዳል ተብሏል፡፡ በምሽቱ ደግሞ በጣይቱ ሆቴል እና በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መሠል ዝግጅቶች ይኖራሉ፡፡ በሌላ በኩል “ሕይወት እዚህ ቦታ” የተሰኘ  የግጥምና ሙዚቃ ዝግጅት ዛሬ ማታ በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ይቀርባል፡፡ ዝግጅቱ አሜሪካ ሀገር ከሚገኘው ጣይቱ ባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ተቀርፆ እዚያው ሀገር በሚገኝ ሬዲዮ ጣቢያ እንደሚተላለፍም ታውቋል፡፡ ከገጣሚዎቹ መካከል ኤፍሬም ስዩም፣ ሰለሞን ሳህለ፣ ዮሐንስ ሐብተማርያም ይገኙበታል፡፡

 

 

 

Read 1220 times Last modified on Saturday, 04 February 2012 12:31