Monday, 31 August 2015 09:00

“ውዳሴ ዲያግኖስቲክስ” ለ500 ሰዎች ነፃ የምርመራ አገልግሎት ሊሰጥ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

     ከተቋቋመ ስድስት ዓመታትን ያስቆጠረውና ልዩ ልዩ የህክምና ምርመራ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ውዳሴ ዲያግኖስቲክስ ማዕከል፤ 500 ለሚሆኑና የመክፈል አቅም ለሌላቸው ህሙማን ነፃ የሲቲስካንና የኤምአርአይ ምርመራ አገልግሎት ሊሰጥ ነው፡፡ማዕከሉ “ጳጉሜን ለጤና” በሚል መርህ በየአመቱ ነፃ የምርመራ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ዘንድሮም ከመንግሥት የህክምና ተቋማት ለሚመጡና አገልግሎቱን በክፍያ ለማግኘት አቅም ለሌላቸው ህሙማን ነፃ የሲቲስካንና የMRI ምርመራ እንደሚያደርግ የማዕከሉ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ኃይሉ ከትናንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል፡፡ ከመንግሥት የጤና ተቋማት የሲቲስካንና የኤምአርአይ ምርመራዎች እንደሚያስፈልጋቸው በሃኪም የተፃፈላቸው ህሙማን ከነሐሴ 22 ጀምሮ በስልክ ቁጥሮች 0111574343 ወይም በሞባይል ቁጥር 0940040404 ደውለው በመመዝገብ፣ ወረፋ መያዝና የነፃ ምርመራው ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
ማዕከሉ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ በየአመቱ በጳጉሜ ተመሳሳይ የነፃ ምርመራ አገልግሎቶችን እየሰጠ ሲሆን ባለፈው ዓመት ለ500 ሰዎች ነፃ የሲቲስካንና ኤምአር አይ ምርመራ አገልግሎት ለመስጠት አቅዶ፣ ለ820 ሰዎች ነፃ አገልግሎቱን እንደሰጠ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የሲቲስካንና የኤምአርአይ ምርመራ አገልግሎት ለማግኘት ከአንድ ሺህ ብር እስከ ሶስት ሺህ ብር ክፍያን እንደሚጠይቅ ይታወቃል፡፡

Read 3525 times