Print this page
Monday, 24 August 2015 10:00

ከምግብ በኋላ ... የማይመከሩ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

ሻይ አይጠጡ
ሻይ በሰውነታችን ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው አሲድ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህ አሲድም በተመገብነው ምግብ ውስጥ ያሉ ፕሮቲኖች እንዲጠነክሩና አልፈጭ እንዲሉ ያደርጋቸዋል፡፡
አያጭሱ ምግብ ከተመገቡ በኋላ ወዲያውኑ ሲጋራ ማጨስ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ከምግብ በኋላ የሚያጨሱ ሰዎች በሳንባ ካንሰር የመያዝ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡
ፍራፍሬ አይመገቡ
ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ ፍራፍሬ መመገብ አንጀታችን በአየር እንዲወጠር ያደርገዋል፡፡ ፍራፍሬ መብላት ከፈለጉ፣ ምግብ ከመመገብዎ ከአንድ ሰዓት በፊት ወይንም ከተመገቡ ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ ቢሆን ይመረጣል፡፡
ገላዎን አይታጠቡ
ምግብ እንደተመገቡ ወዲያውኑ ገላን መታጠብ በእግርና በእጃችን አካባቢ የደም ፍሰት (ዝውውር) መጠኑን እንዲጨምር የሚያደርግ ሲሆን ይህም በሆዳችን አካባቢ ያለውን የደም ፍሰት ይቀንሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያትም የምግብ ስልቀጣ ስርዓቱ ይዳከማል፡፡
ቀዝቃዛ ውሃ አይጠጡ
ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃ መጠጣት በበላነው ምግብ ውስጥ የሚገኙትን ዘይት ነክ ነገሮች ወደ ጠጣርነት ይቀይራቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ የምግብ መፈጨት ሂደቱን ከማጓተቱም በላይ ወደ ጠጣርነት የተቀየረው ዘይትና ቅባት ጨጓራ ውስጥ ከሚገኝ አሲድ ጋር በመገናኘት በፍጥነት ተሰባብሮ ወደ አንጀት ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል፡፡ ይህም ወደ ስብነት ተቀይሮ ለካንሰር መከሰት ሰበብ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህም በተቻለዎ መጠን ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃን ከመጠጣት ይቆጠቡ፡፡ በምትኩ ለብ ያለ ውሃ ቢጠጡ የምግብ መፈጨት ሥርዓቱ የተሳካ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡
የእግር ጉዞ አያድርጉ
ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ የእግር ጉዞ ማድረግ የምግብ ስልቀጣ ሂደቱ በአግባቡ እንዳይከናወን ያደርገዋል፡፡
ወዲያውኑ አይተኙ
በልተን ወዲያውኑ ከተኛን የተመገብነው ምግብ በአግባቡ አይፈጭም፡፡ ይህ ደግሞ ለጨጓራ ህመምና ለአንጀት ቁስለት ይዳርገናል፡፡

Read 7702 times
Administrator

Latest from Administrator