Monday, 24 August 2015 09:25

መንግስት፤ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ሥጋ ቤቶች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

Written by  ማህሌት ኪዳነወልድ
Rate this item
(6 votes)

    በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ  ከነሐሴ 1 ጀምሮ ለ15 ቀናት ሲፆም የቆየው የፍልሰታን ፆም መፈታት ተከትሎ በሥጋ ዋጋ ላይ ጭማሪ የሚያደርግ ማንኛውም ሥጋ ቤት ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድበት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ገመቺስ መላኩ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ በፆም ፍቺው ምክንያት በየቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር በኩል የሥጋ እጥረት እንዳይፈጠር ከበቂ በላይ በሬዎች የተገዙ ሲሆን በዓሉን ሰበብ በማድረግ ዋጋ የሚጨምሩ ካሉ ጥብቅ አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በማህበራቸው በኩል ተጠያቂ ይሆናሉ ብለዋል - ኃላፊው፡፡ ከሥጋ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክፍተት እንደማይፈጠር ያረጋገጡት አቶ ገመቺስ፤ ህብረተሰቡ የዋጋ ጭማሪ ካጋጠመው
በ8588 ደውሎ ጥቆማ በማድረስ፣ በንግድ ስርአት ውስጥ የሚታየውን ህገ-ወጥነት ሊታገል እንደሚገባው አበክረው አሳስበዋል፡፡

Read 2963 times