Saturday, 01 August 2015 14:48

የየአገሩ ምሳሌያዊ አባባል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሴት ውበት የክረምት ሌሊትን አያሞቅም።
የዩክሬናውያን አባባል
ውሻ ጭራውን ካልረገጥከው በስተቀር አይነክስህም፡፡
የካሜሩያውያን አባባል
ጓንት ያጠለቀች ድመት አይጥ አትይዝም፡፡
የፈረንሳውያን አባባል
የተውሶ ድመት አይጥ አትይዝም፡፡
የጃፓናውያን አባባል
ትኩረት የሚስቡ ሴቶች ከኋላህ እንዲጓዙ አትፍቀድ፡፡
የካምቦዲያውያን አባባል
ከነገ ጫጩት የዛሬ እንቁላል ይሻላል፡፡
የቬትናማውያን አባባል
ዘማሪ ወፍ መዝሙር እየበላች አትኖርም፡፡
የሩሲያውያን አባባል
አሪፍ ውሻ ተሳስቶ አይጮህም፡፡
የፈረንሳውያን አባባል
ማለፊያ የወይን ጠጅ የያዘ ፋሽኮ ቡሽ አይፈልግም፡፡
የፈረንሳውያን አባባል
ቀበሮ በተመሳሳይ ወጥመድ ሁለቴ አይያዝም፡፡
የላቲን አባባል
 ሞኝ በራሱ ይስቃል፡፡
የናሚቢያውያን አባባል
እግዚአብሔር በሳቅ እንዲፈርስ ከፈለግህ ዕቅድህን ንገረው፡፡
የናሚቢያውያን አባባል
ህፃን፤ እግሮቹ በጨመሩ ቁጥር ክንፎቹ የሚቀንሱ መላዕክ ነው፡፡
የፈረንሳውያን አባባል
አፍህ ቢላዋ ከሆነ ከንፈርህን ይቆርጠዋል፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
እግዚአብሔር አንድን አገር መቅጣት ሲፈልግ፣ መሪዎቹን ጥበብ ይነፍጋቸዋል፡፡
የጣልያኖች አባባል

Read 1674 times