Saturday, 01 August 2015 14:41

“የነገርኩሽ ዕለት” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 በዳንኤል ንጉሴና ዮሐንስ ሙሉጌታ ተፅፎ፣ በመልካሙ ማሞ ዳይሬክት የተደረገው “የነገርኩሽ ዕለት” ፊልም በነገው ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡
የፊልሙ ታሪክ፤ አባት ለልጁ የሚከፍለው መስዋዕትነት የሚታይበትና ጊዜያዊ ችግርን ለማለፍ ተብሎ የተዘየደው መላ ኋላ እውነቱ ሲታወቅ የሚያስከትለውን የህይወት ውጣ ውረድ የሚያስቃኝ ነው ተብሏል፡፡
በፊልሙ ላይ፤ ደሳለኝ ኃይሉ፣ አሸናፊ ማህሌት (ይበቃል)፣ ችሮታው ከልካይ፣ ዋሲሁን በላይና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ የ1፡38 ደቂቃ ርዝመት ያለውን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ 1 ዓመት እንደፈጀ ፕሮዱዩሰሩ ደስይበልህ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ገልጿል፡፡

Read 1776 times