Saturday, 01 August 2015 14:40

የሩሲያ የህፃናት መፃህፍት ለት/ቤቶች ይበረከታሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በሩሲያ ህፃናት ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፉት “ዶ/ር አይቦሊት” እና “ቫክሳ ክሊያክሳ” የተሰኙ የህፃናት መፃህፍት ወደ አማርኛ ተተርጉመው በትላንትናው ዕለት ምሽት በሩሲያ የሳይንስና ባህል ማዕከል የተመረቁ ሲሆን በኢትዮጵያ ለሚገኙ ህፃናት እንዲደርሱ በየት/ቤቱ በስጦታ እንደሚበረከቱ ታውቋል፡፡
መፃህፍቱን ወደ አማርኛ የተረጎሙት በሞስኮ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መምህር የሆኑትና በርካታ የሩሲያ ሥነ-ፅሁፎችን ወደ አማርኛ በመመለስ የሚታወቁት ፕሮፌሰር ንጉሴ ካሣዬ ወልደሚካኤል ናቸው ተብሏል። ሁለቱ መፃህፍት ወደ አማርኛ ተተርጉመው ለኢትዮጵያ ህፃናት እንዲዳረስ “ሩስኪ ሚር” የተባለ የሩሲያ ተቋም ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡  

Read 1571 times