Monday, 27 July 2015 11:28

በዘንድሮው የሮቦቶች የአለም ዋንጫ ጃፓን አሸነፈች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  እ.ኤ.አ በ2050 ሮቦቶችንና ሰዎችን ኳስ ለማጋጠም ታቅዷል
    በቻይና በተከናወነውና 40 የአለማችን አገራት ቡድኖች በተካፈሉበት የዘንድሮው የአለም ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ጃፓን ማሸነፏን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በጃፓኑ ቺባ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ የተሰሩ ሮቦቶችን የያዘው ዘ ብሬንስ ኪድስ የተባለው የጃፓን የሮቦቶች ቡድን፣ የቻይናውን ዚጁዳንሰር አቻውን አንድ ለባዶ በማሸነፍ ነው ዋንጫውን ለመሳም የበቃው፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር እ.ኤ.አ ከ1997 ጀምሮ በየአመቱ ሲከናወን እንደቆየ ያስታወሰው ዘገባው፣ በውድድሩ የሚሳተፉ አገራት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም ጠቁሟል፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በሮቦቲክስ ዘርፍ የተሻለ ፈጠራን የማበረታታትና የማስፋፋት አላማ እንዳለው የጠቀሰው ዘገባው፣ እ.ኤ.አ በ2050 በሮቦቶችና በሰዎች መካከል የእግር ኳስ ውድድር የማካሄድ  እቅድ መያዙንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2596 times