Monday, 27 July 2015 11:20

የቴዎድሮስ ተ/አረጋይ አዲስ ቲያትር ረቡዕ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

“የቤት ሥራ” የቴሌቪዥን ድራማ በቅርቡ መታየት ይጀምራል
   በጋዜጠኛና ፀሐፌ ተውኔት ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተደርሶ፣ በካሌብ ዋለልኝ የተዘጋጀው “ከትዳር በላይ” የተሰኘ ዘመናዊ ኮሜዲ ቲያትር የፊታችን ረቡዕ  ከ11፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡ ቲያትሩ በየሳምንቱ ዘወትር ረቡዕ በተመሳሳይ ሰዓት በዚሁ ቴአትር ቤት እንደሚታይ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ እና በሰዓዳ መሃመድ ተደርሶ፣ በኢሳያስ ግዛው የሚዘጋጀው “የቤት ሥራ” የቴሌቪዥን ድራማ፣በያዝነው ወር መጨረሻ ላይ በኢቲቪ-1 መታየት እንደሚጀምር ተገለፀ፡፡ በቴዎድሮስ የትያትር ኢንተርፕራይዝ ፕሮዱዩሰርነት የሚቀርበው የቲቪ  ድራማ፤ በትዳርና በቤተሰብ ግንኙነት ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡ በድራማው ላይ አርቲስት ሽመልስ አበራ፣ ሰላም ተፈሪ፣ ስዩም ተፈራ፣ ቶማስ ቶራ፣ ጀምበር አሰፋ፣ ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ) እንደሚተውኑበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 3049 times