Monday, 27 July 2015 11:20

“ኑሮ እና ፖለቲካ ቁጥር 3” ለንባብ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በወግ ፀሐፊነቱ የሚታወቀው በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር የጻፋቸው በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መጣጥፎች የተካተቱበት “ኑሮ እና ፖለቲካ- ቁ 3” የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ ትትሞ ለንባብ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ ቀላል የማይባሉ አዳዲስ ሥራዎች እንደተካተቱበት የጠቆመው ደራሲው፤ ቀድሞ የተሰሙና የተደመጡትም እንኳ በደጋሚ እንዲነበቡ ተደርገው በደንብ መቃናታቸውንና አዳዲስ ነገር እንደተጨመረባቸው ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡ በ157 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ለአገር ውስጥ በ40.50፣ለውጭ አገር በ15 ዶላር ይሸጣል፡፡  ደራሲው ከዚህ ቀደም “መንታ መልኮች”፣ “ኑሮ እና ፖለቲካ” (ቁጥር 1 እና 2) የሚሉ መጻህፍትን ያሳተመ ሲሆን በተለያዩ የፕሬስ ውጤቶች ላይ በአሽሙር የተጠቀለሉ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ወጎችን በማቅረብም ይታወቃል፡፡

Read 1414 times