Saturday, 18 July 2015 10:19

መድረክና ሰማያዊ፤ በአባሎቻችን ላይ ግድያና እስር እየተፈፀመ ነው ሲሉ አማረሩ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

    ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከግንቦቱ ምርጫ በኋላ አባሎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ላይ ግድያ፣ እስራትና እንግልት እየተፈፀመባቸው መሆኑን የገለፁ ሲሆን መድረክ 5 አባሎቹ እንደተገደሉበት ስታውቋል። ሰማያዊ ፓርቲም በአባላቱ ላይ እየተፈፀመ ነው ያለው ግድያ፣ እስርና እንግልት በአስቸኳይ እንዲቆም ሰሞኑን ጠይቋል፡፡ ድረክ በሰጠው በመግለጫ፤ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች በአባላቱ ላይ የሚፈፀሙት እስራቶችና
ንግልቶች ተጠናክረው እንደቀጠሉ አመልክቷል፡፡ ከምርጫው በኋላ በትግራይ፣ በኦሮሚያ እና ቡብ ክልል ከተገደሉት 4 የመድረክ አባላት በተጨማሪ ሰኔ 27 ቀን በደቡብ ክልል በከፋ ዞን፣ ቢግንቦ ወረዳ፣ በኢዲዩ ካካ የምርጫ ክልል፣ በጎጀብ ምርጫ ጣቢያ የመድረክ ታዛቢ የነበሩት አቶ አስራት ኃይሌ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ግድያ እንደተፈፀመባቸው መድረኩ ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡
የሟቹ አስከሬን ከቀብር ቦታ ጋር በተያያዘም ከፍተኛ እንግልት አጋጥሞት እንደነበር የጠቀሰው መድረክ፤  እስከ ሐምሌ 1 ቆይቶ በህብረተሰቡ ትብብር የቀብር ስነ-ስርአቱ ሊፈፀም መቻሉን አስታውቋል፡፡ በተለያዩ የደቡብና የኦሮሚያ ዞኖችና ወረዳዎች በምርጫው የመድረክ ታዛቢ ወኪሎች የነበሩ፣ አባላት እና ደጋፊዎች ከፓርቲው ጎን በመቆማቸው ብቻ የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዳያገኙ ከመደረጉም በላይ ከፓርቲው አባልነት ራሳቸውን እንዲያገሉ ግፊት እየተደረገባቸው ነው ብሏል - መድረክ፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ፤ “የወለደውን የረሳ ብሶት የወለደው ስርአት! የዘመቻ እስርና ግድያ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡” በሚል ሰሞኑን በፅ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ በግንቦቱ ምርጫ ማግስት በምርጫው በንቃት ይሳተፉ የነበሩ ዜጎች እየታደኑ እየታሰሩ ነው ብሏል፡፡ ፓርቲው፤ ዜጎችን በፖለቲካ አመለከታቸው ሳቢያ ከስራ ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማሸማቀቅና ማንገላታት እንዲቆም አበክሮ ጠይቋል።
“በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የሰማያዊ፣ የመኢአድ፣ የቀድሞ አንድነት፣ የመድረኩና ሌሎችም የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ኢላማ ተደርገው እየተሳደዱና በጅምላ እየታሰሩ እንዲሁም በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ ይገኛሉ” ብሏል - ፓርቲው በመግለጫው፡፡ ከምርጫው ማግስት ጀምሮ በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ እየደረሰ ነው ያለው ግድያ፣ እስርና እንግልትም በአስቸኳይ እንዲቆም ሰማያዊ ፓርቲ ጠይቋል፡፡  

Read 2735 times