Saturday, 18 July 2015 10:13

ሃይሌ በኬንያው የ836 ኪሎ ሜትር ጉዞ ይሳተፋል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

    አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ በኬንያ ሰላምን ለማስፈን ታስቦ በተዘጋጀውና በአጠቃላይ 800 ኪሎ ሜትሮችን በሚሸፍነው የሰላም ጉዞ የተሰኘ የታዋቂ አትሌቶች የእግር ጉዞ ላይ እንደሚሳተፍ ዘ ጋርዲያን ረቡዕ ዘገበ፡፡“የዜጎች መገደልና ከመኖሪያ ቤታቸው መፈናቀል በሁላችንም ልብ ውስጥ ጥልቅ ሃዘን የሚፈጥር ነገር ነው” ሲል ባለፈው ሳምንት ለጉዳዩ የሚሰጠውን ትኩረት ያሳወቀው ሃይሌ፣ በኬንያ ሰላምን ለማስፈን ታስቦ በሚከናወነው የሰላም ጉዞ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚሳተፍ መግለጹንም ዘገባው ገልጧል፡፡ኬንያውያን ሰላምን ጠቀሜታ እንዲገነዘቡና በተለይም በአገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢዎች የሚታየውን የጎሳ ግጭት ለመግታት የሚያስችል አገራዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀው ይህ የሰላም ጉዞ፣ በመጪው ነሃሴ ስድስት ቀን የሚጠናቀቅ ሲሆን ሃይሌም በእለቱ በሚደረገው የመጨረሻው ጉዞ እንደሚሳተፍ ይጠበቃል፡፡
የማራቶን የአለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነውን አትሌት ፖል ቴርጋት ጨምሮ ታዋቂ ኬንያውያን
አትሌቶች የሚካፈሉበት ይህ የሰላም ጉዞ፣ በሰሜናዊቷ የኬንያ ከተማ ሎድዋር ባለፈው ረቡዕ የተጀመረ ሲሆን፣ ለ24 ተከታታይ ቀናት በየቀኑ 40 ኪሎ ሜትሮችን በመሸፈን በአጠቃላይ 836 ኪሎ ሜትሮችን ይሸፍናል ተብሏል፡፡አትሌቶቹ በጉዞው ከ250 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ በማሰባሰብ በአገሪቱ ተለያዩ አካባቢዎች ለሚከናወነው የሰላም ማስፈን ፕሮግራም ለመለገስ ማቀዳቸውንም ዘ ጋርዲያን አክሎ ገልጧል፡፡በህገወጥ የሰዎች ዝውውር የተጠረጠሩ 15 ኢትዮጵውያንን በኬንያ ታሰሩበኬንያ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ተግባር ላይ ተሰማርተው ሲንቀሳቀሱ ነበር ተብለው የተጠረጠሩ 15 ኢትዮጵውያን ባለፈው ረቡዕ ኢምቡ በተባለችው የኬንያ ከተማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢንቲቪ ኬንያ ዘገበ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአገሪቱ መዲና ናይሮቢና በኢምቡ ከተማ አካባቢ በስውር በህገወጥ መንገድ ሰዎችን ሲያዘዋውሩ እንደነበር የጠቆመው ዘገባው፣ ፖሊስ የደረሰውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ ባደረገባቸው ክትትል እንደዛቸው ገልጧል፡፡የከተማዋ ፖሊስ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት ጥቆማ ተጠርጣሪዎቹን በአንድ የበቆሎ እርሻ ውስጥ ተደብቀው እንዳሉ በቁጥጥር እንዳዋላቸውና ኢትዮጵውያን መሆናቸውን ከመግለጽ ውጭ፣ ስለተጠርጣሪዎቹ ማንነት መረጃ አልሰጠም፡፡

Read 2115 times