Saturday, 11 July 2015 12:35

የአዲስ ዓመት ኤክስፖ ከ15 ሚ. ብር በላይ ወጪ ይደርግበታል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በዓለም ትልቁን የእንቁጣጣሽ ፖስት ካርድ በጊነስ ቡክ ለማስመዘገብ ታቅዷል

የዘንድሮው የ“ሀበሻ አዲስ ዓመት ኤክስፖ 2008” ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበትና ኤግዚቢሽኑን ከቀደምቶቹ የተለየ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡
የኤግዚቢሽኑ አዘጋጅ የሀበሻ ዊክሊ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አደኒክ ወርቁ ሰሞኑን በሀርመኒ ሆቴል ለጋዜጠኞች በተሰጠ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ከዘጠኝ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ዋጋ ጨረታውን አሸንፈው ማዕከሉን ለአዲስ ዓመት ኤክስፖ የያዙት ሲሆን በኤግዚቢሽኑ ከዚህ ቀደም ያልተለመዱና ለየት ያሉ ፕሮግራሞችን ለማዘጋጀት ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ጨረታውን 50 በመቶ ጭማሪ አድርገው ማሸነፋቸውን የተናገሩት አቶ አዶኒክ፤ በቦታ ሽያጭ ላይ ያደረጉት ጭማሪ ግን ከ7 በመቶ በታች መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ በቀን ከ500 ሺህ በላይ ጎብኚ ይኖረዋል ተብሎ በሚጠበቀው የአዲስ ዓመት ኤክስፖ ዝግጅት፣ ከአሁን በፊት ያልተሞከሩና በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ሊያስመዘግቡ ይችላሉ የተባሉ ነገሮች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፣ ከእነዚህ መካከል በጥንታዊው ብራና የተዘጋጀ በዓለም ትልቁ የእንቁጣጣሽ ፖስት ካርድና የዓለማችን ትልቁ የሻማ ዛፍ እንደሚገኙበት ተናግረዋል፡፡
ከ100 በላይ ድምፃውያን፣ኮሜዲያን እንዲሁም ቀደምትና ዘመናዊ የሀገሪቱ ስመጥር ባንዶች በኤግዚቢሽኑ ላይ እንደሚሳተፉ የተገለጸ ሲሆን ታዋቂውና አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሣም ሥራዎቹን በኤክስፖው ላይ እንደሚያቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

Read 1477 times