ቤትና ንብረቶችን በኢንተርኔት ለመሸጥና ለመግዛት የሚያስችል ዘመናዊ የግብይት ሥራ የሚሰራና ላሙዲ የተባለ አለምአቀፍ የኦንላይን ሪልስቴት ኩባንያ ሥራ ጀመረ፡፡
ደንበኞች ንብረታቸውን በቀላሉ ለመሸጥና ለመግዛት ያስችላቸዋል የተባለውና ዘመናዊው የኢንተርኔት የመገበያያ መንገድ ሥራ መጀመሩን አስመልክቶ ከትናንት በስቲያ በኩባንያው ቢሮ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው በአገሪቱ የሪል ስቴቶች መስፋፋትና ማደግ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ እያሳየ መጥቷል፡፡ ስለዚህም ደንበኞች ስለሚፈልጓቸው ቤቶችና ንብረቶች በቂና ጥልቀት ያለው መረጃ ለማግኘት የሚችሉበት መንገድ በስፋት ሊኖር ይገባል፡፡
ኩባንያው በገዢና ሻጭ በኦንላይን ተገናኝተው ቤትና ንብረታቸውን ለመገበያየት እንዲችሉ ዕድሉን ያመቻቻል፡፡
ኩባንያው ከዚህ በተጨማሪ ዳያል 4 ሆም የተሰኘ ሆት ላይንን ያስተዋወቀ ሲሆን ይህም ሆትላይን ንብረት ፈላጊዎች ያለ ኢንተርኔት ትስስር ተጠቃሚዎችን በስልክ እንዲገናኙ ለማድረግ የሚያስችል አሠራር ማዘርጋቱንም በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል፡፡
ላሙዲ በኬንያ፣ በታንዛኒያ፣ በናይጀሪያ፣ በጋና፣ በኡጋንዳና ሩዋንዳ ቢሮዎቹን ከፍቶ እየሠራ የሚገኝ ኩባንያ ነው፡፡
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ