Saturday, 11 July 2015 11:32

የኮሪያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ሆኖበታል ተብሏል
ኮሪያ ሆስፒታል ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ የሰራው የሆስፒታሉ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በትላንትናው ዕለት ተመረቀ፡፡ ሆስፒታሉ በኮሪያ ዘመቻ ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን ዘማቾች ላደረጉት አስተዋፅኦ እንደ ምስጋና ሆኖ እንዲሰራና አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ እ.ኤ.አ በህዳር ወር 2004 ዓ.ም መመስረቱን የገለፁት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ኪም ቹልሱ፤ዛሬ በአገሪቱ በህክምናው ዘርፍ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ የህክምና ባለሙያዎችና ዘመናዊ መሳሪያዎች የሚገኙበት ታላቅ ሆስፒታል ለመሆን መብቃቱን ገልፀዋል፡፡ እስከአሁን በአገሪቱ ውስጥ የማይሰጡ የተለያዩ የህክምና አይነቶችን ጨምሮ ከ20 በላይ ዲፓርትመንቶችን ያቀፈው አዲሱ የማስፋፊያ ፕሮጀክት፣እጅግ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችና ከ60 በላይ VIP አልጋዎችን መያዙን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ሆስፒታሉ ሲቋቋም ይዞት ከነበሩ ዕቅዶች ሁለተኛው ሲሆን ተግባራዊ መሆን ከሚገባው ጊዜ በጥቂት አመታት መዘግየቱ ተጠቁሟል፡፡ ቀጣዩ የሆስፒታሉ ዕቅድ (Third phase) መንትያ ህንፃዎችን መገንባትና የሆስፒታሉን አስተዳደርና ስራውን ሙሉ በሙሉ ለኢትዮጵያውያን ማስረከብ እንደሆነም በዚሁ ወቅት ተገልጿል፡፡

Read 2838 times