ድምፃቸው ጠፍቶ የከረሙት ወጣቶቹ የጃኖ ባንድ የሙዚቃ አባላት ከሚቀጥለው ሳምንትጀምሮ በክለብ H20 ማቀንቀን የሚጀምሩ ሲሆን ለመዲናዋ የመጀመሪያ ነው የተባለውን የሮክሙዚቃ ለታዳሚዎች ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ባንዱ ከተቋቋመ ወዲህ በምሽት ክለብ የሙዚቃ ሥራውን ሲያቀርብ የአሁኑ የመጀመሪያውእንደሚሆን ታውቋል፡፡የባንዱ አባላት ሁለተኛ የሙዚቃ አልበማቸውን በሦስት ወራት ጊዜ ወስጥ እንደሚለቁምለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች ለ1 ወር የሙዚቃ ኮንሰርት ያቀርባሉ
ተብሏል፡፡ የጃኖ ባንድ አባላት ተለያይተዋል በሚል ሲናፈስ የቆየውን ወሬ መሰረተቢስ ነው
በሚል ባንዱ አስተባብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና