የጆሊ ጁስ አምራች የሆነው ቴስቲ ፉድስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግ. ኩባንያ፤ በጥራት የስራ አመራር ብቃት ጥራቶችን አሟልቶ አለማቀፉን የISO 9001/2008 ሰርተፊኬት ተሸላሚ መሆኑን የኩባንያው ሃላፊዎች ገለጹባ የተለያዩ የሚበጠበጡ የዱቄት ጣፋጭ መጠጦችንና ቴስቲ ስናክን የሚያመርተው ኩባንያው፤ የአለማቀፉ ጥራት ተሸላሚ መሆኑ፣ ምርቶቹን ወደ አለማቀፍ ገበያ ይዞ እንዲቀርብና ተቀባይነት እንዲያገኝ ይረዳዋል ተብሏል፡፡ ከ8 ዓመት በፊት የተቋቋመው ኩባንያው፤ታዋቂውን የጆሊ ጁስ መጠጥ ጨምሮ የተለያዩ የፍራፍሬ ጣዕም ያላቸውን በውሃ ተበጥብጠው የሚጠጡ ፍሌቨሮች የሚያመርት ሲሆን ደረቅ ቴስቲ ስናክ በማምረትም ከሃገር ውስጥ በተጨማሪ ለውጪ ገበያ እንደሚያቀርብ ተጠቁሟል፡፡
ኩባንያው ለወደፊት የምርቶቹን የጥራት ደረጃ ጠብቆ በኢትዮጵያ ያለውን የገበያ አድማስ ለማስፋት እንደሚተጋ የስራ ኃላፊዎቹ ገልፀዋል፡፡
Published in
ዜና