Saturday, 04 July 2015 09:25

የሰማያዊ ፓርቲ አባሉን ገድሏል የተባለው የ19 ዓመት እስር ተፈረደበት

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
Rate this item
(0 votes)

     ባለፈው ግንቦት በተካሄደው 5ኛው አገራዊ  ምርጫ ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደብረማርቆስ ከተማ ተወዳድሮ የነበረውን ወጣት ሳሙኤል አወቀን ገድሏል በተባለው ተከሳሽ ላይ ፍርድ ቤት የ19 ዓመት ፅኑ እስራት ፈረደበት፡፡ የምሥራቅ ጐጃም ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ከትናንት በስቲያ በሰጠው ውሳኔ፣ ሟች ሳሙኤል አወቀን በመደብደብ ለህልፈት ዳርጐታል በሚል ወንጀል ክስ በተመሰረተበት ተቀበል ውዱ ላይ የአስራ ዘጠኝ ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል፡፡ ተከሳሹ ገንዘብ ወስዶ አስቀርቶብኛል በሚል ምክንያት ከሟች ጋር ግጭት መፍጠሩንና በዚህ ምክንያትም ከግብረአበሩ ጋር በመሆን ሟችን ደብድቦ ለሞት እንዳበቃው የአቃቤ ህግ ክስ ያመለክታል፡፡ ለወንጀሉ ተባባሪ የሆነው ተጠርጣሪ እስከአሁን ድረስ አለመያዙም ተጠቁሟል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የፍ/ቤቱን ውሳኔ፤ በወንጀሉ ውስጥ ተሣትፏል የተባለው ተባባሪ ባልተያዘበት ሁኔታ በአስራ ሰባት ቀናት ውስጥ በተሰጠው የፍርድ ውሣኔ ቅሬታ እንዳለው ገልጿል፡፡ በአዲስ አበባ ለወራት በእስር ተይዘው የሚማቅቁ የፓርቲው አባላት እስከአሁን ምንም አይነት ውሣኔ እንዳልተሰጣቸው ፓርቲው ጠቁሟል፡፡

Read 1626 times